Tender Notice Board
Discover the latest public procurement and private sector tenders from across Ethiopia. Register to unlock full details.
Search Tenders
አምባሰል የንግድ ሥራዎች ኃ.የተ.የግል ማህበር ሸቀጥና ሸቀጥ ነክ ያልሆኑ ልዩ ልዩ ንብረቶችን በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል::
ቀን 18/08/2018 የጨረታ ማስታወቂያ አምባሰል የንግድ ሥራዎች ኃ.የተ.የግል ማህበር ሸቀጥና ሸቀጥ ነክ ያልሆኑ ልዩ ልዩ ንብረቶችን በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል:: በመሆኑም የዚህን ጨረታ ሰነድ በተገለፀው አድራሻ በመግዛት ማንኛውም ተወዳድሮ ያሸነፈው አካል እቃዎቹን መግዛት የሚችል ሲሆን:- የጨረታ አይነት፡– የውሃ ፓምፕና መለዋወጫ፣ ጄነሬተርናመለዋወጫዎች፣የመኪና ጎማ ፣ካመነዳሪ፣ፍላፕ ፣የመኪና ባትሪ፣ኮፒውተር፣ ፕሪንተር ስልክና ሌሎች ተያያዥ ዕቃዎች፤ አገልግሎት የማይሰጡ በፀሃይ የሚሰሩ ፋኖሶች ፣መለዋወጫዎች አገልግሎት የማይሰጡ የቢሮ እቃዎች፣የቢሮና የፅህፈት መሳሪያዎች እጣን የተለያዩ ብረታ ብርቶች፣ ወኪንግ ትራክተር አገልግሎት የማይሰጡ ልዩ ልዩ የጥራጥሬ ማበጠሪያ ማሽነሪዎች፣ ልዩ ልዩ እቃዎች በሚል በተለዩት የጨረታ ሰነዶች በጥቅል (በሎት/ LOT) አደራጅቶ ገዥዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ የተዘጋጀ የጨረታ ሰነድ ነው፤ ማንኛውም ተጫራች (የተፈጥሮም ይሁን ሕጋዊ ሰውነት ያለው) በአንድ የጨረታ ሎት /Lot/አይነት ከአንድ በላይ የጨረታ ሰነድ ገዝቶና ሞልቶ ማስገባት አይችልም፡፡ ሆኖም ሻጭ ለሽያጭ ባወጣቸው የተለያዩ ሎቶች ላይ በሁሉም ላይ በመሳተፍ ዋጋ ማቅረብ ይችላል፡፡እያንዳንዱ ተጫራች በተመሳሳይ ሎት (በአንድ ሎት) ላይ ከአንድ በላይ የጨረታ ሰነድ ሞልቶ ማቅረቡ ከተረጋገጠ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከውድድር ውጭ ይደረጋል፡፡ ሻጭ ይህንን ጨረታ ሰነድ በመሸጡ ምክንያት በማንኛውም ሁኔታ የውል ስምምነት እንዲፈጽም አያስገድደውም፡፡ የውል ስምምነት እንደያዘም አይቆጠርም፡፡ ተጫራቾች ለመግዛት ዋጋ የሰጡበትን የንብረት አይነት ወይም የሎት አይነት ጠቅላላ ዋጋ 5% የጨረታ ማስከበሪያ (Bid Bond) በባንክ በተረጋገጠ ቼክ (CPO) ወይም ጥሬ ገንዘብ በማስያዝ ከጨረታ ዋጋ ሠነዳቸው ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል ፡፡ ተጫራቾች በኩባንያው ዋና መ/ቤት የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል በአቅራቢያው በሚገኘው ሻጭ አድራሻ ማለትም አዲስ አበባ ወሎ ሰፈር ከሚገኘው አምባሰል ንግድ ስራዎች ድርጀት ኃየተ/የግ ማህበር ህንጻ 5ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 503 ፣በመምጣት መግዛት ይችላሉ፡፡ ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ለመግዛት በሚመጡበት ጊዜ ኢትዮጵያዊ ወይም የውጭ ዜጋ ለመሆናቸው ማንነታቸውን የሚገልፅ መታወቂያ ወይም ፓስ ፖርት ኮፒ እንዲሁም የንግድ ድርጅቶች ከሆኑ የንግድ ስራ ፈቃድና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡ ጨረታው አየር ላይ የሚቆየው በጋዜጣ ከታወጀበት እለት 18/08/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የስራ ቀናት ሲሆን ጨረታው በ15ኛው ቀን ማለትም በ05/09/2018 ከቀኑ 4፡00 ሰዓት የጨረታ ሣጥኑ ይታሸጋል:: የኩባንያው ንብረት አስወጋጅ ኮሚቴ በእለቱ ከጠዋቱ 5፡00 ሰዓት በሻጭ አድራሻ ማለትም አዲስ አበባ ወሎ ሰፈር ከሚገኘው አምባሰል ህንጻ 3ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 305 የጨረታ ሰነድ የመከፈት ስነ- ስርዓቱን መከታተል የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ በጨረታ ሰነድ የመከፈት ስነ-ስርዓቱ ላይ የተጫራቾች ያለመገኘት ጨረታውን ዋጋ አያሳጣውም፡፡ ተጫራቾች በዚህ ጨረታ ለመሳተፍ ለሚያወጡት የትኛውም ዓይነት ወጭ (በጨረታው ተሳትፎ ቢያሸንፍ፣ ቢሸነፍ፣ በተለያየ ምክንያት ከጨረታው ውጭ ቢደረግ ወይም ጨረታው ቢሰረዝ) ሻጭ ተጠያቂ አይሆንም፡፡ በጨረታ ሰነዶቹ ላይ ማብራሪያ የሚፈልግ ተጫራች በዚህ የጨረታ ሰነድ ላይ በተመለከተው የሻጭ አድራሻ የሚፈልገውን ማብራሪያ በፅሑፍ መጠየቅ ይችላል፡፡ ተጫራቾች የ
Closing Date
Check Details
የእናት ባንክ አ.ማ ለሰጠው ብድር በዋስትና የያዘውንና ከዚህ በታች በሰንጠረዡ የተመለከተውን ንብረት ባለበት ሁኔታ በአዋጅ ቁጥር 1147/2011 ለባንኮች በተሰጠው ስልጣን መሰረት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የሐራጅ ማስታወቂያ የእናት ባንክ አ.ማ ለሰጠው ብድር በዋስትና የያዘውንና ከዚህ በታች በሰንጠረዡ የተመለከተውን ንብረት ባለበት ሁኔታ በአዋጅ ቁጥር 1147/2011 ለባንኮች በተሰጠው ስልጣን መሰረት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ ተ.ቁ የተበዳሪ ስም የንብረት አስያዥ ስም አበዳሪው ቅርንጫፍ ለጨረታው የቀረበው ንብረት የንብረቱዝርዝር የሐራጅ መነሻ ዋጋ በብር ሐራጁ የሚከናወንበት ቀንና ዓ.ም ሰዓት የሰሌዳ ቁጥር የስሪት ዘመን የሞተር ቁጥር የሻንሲ ቁጥር 1 አቶ ደሳለኝ ተፈራ ቢሰጥ አቶ ደሳለኝ ተፈራ ቢሰጥ ንግስት እሌኒ ሳሪስ ሱዙኪ ዲዛየር አአ- 3-B48458 2021 K12MP4310503 MBHZF6C1XNG191819 2,300,000.00 መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ/ም ከጧቱ 3:00-4:15 የሐራጅ ደንቦች 1 ተጫራቾች የሐራጁን መነሻ ዋጋ አንድ አራተኛ (¼ኛ) በባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲ.ፒ.ኦ) ብቻ በማስያዝ መጫረት ይችላሉ፡፡ 2 የተጫራቾች ምዝገባ ከሐራጅ መዝጊያ ሰዓት አስራ አምስት ደቂቃ በፊት ይጠናቀቃል፡፡ በሐራጁ የመጨረሻ አስራ አምስት ደቂቃዎች የተጫራቾች ምዝገባ አይካሄድም፡፡ 3 አሸናፊ የሆነው ተጫራች ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ የጨረታው አሸናፊ መሆኑ ደብዳቤ ከደረሰው ቀን ጀምሮ በአስራ አምስት (15) ቀናት ውስጥ አጠቃልሎ መከፈል አለበት፡፡ ባይከፍል ግን ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ሐራጁ ይሰረዛል፡፡ 4 ሐራጁ ከላይ በተገለፀው ቀንና ሰዓት ንብረቶቹ ባሉበት በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ ሰንጋተራ ተብሎ በሚታወቀው በባንኩ የወደፊት ዋና መ/ቤት ህንፃ መገንቢያ ቦታ ይከናወናል፡፡ 5 በሐራጅ ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች፣ ተበዳሪ እና ንብረት አስያዥ ወይም ሕጋዊ ተወካዮች ብቻ ናቸው፡፡ 6 በተሸከርካሪው ላይ ለመንግስት የሚከፈለው 15% የተ.እ.ታክስ እና ገዢ እንዲከፍላቸው በህግ የተወሰኑ ክፍያዎችን የስም ማዛወሪያ ጨምሮ ገዢው / አሸናፊው ይከፍላሉ፡፡ 7 ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 8 ለሐራጅ የቀረበውን ንብረት ለመጎብኘት የሚፈልጉ ከአበዳሪው ቅርንጫፍ ጋር ቀጠሮ በመያዝ መጎብኘት ይችላሉ፡፡ 9 ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 011-5-58-65-68 በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡፡
Closing Date
Check Details
አቢሲንያ ባንክ /አ.ማ/ የሰጠው ብድር ባለመከፈሉ የብድር መያዣ ንብረቶቹ ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ አቢሲንያ ባንክ /አ.ማ/ የሰጠው ብድር ባለመከፈሉ የብድር መያዣ ንብረቶቹ ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ ተ.ቁ የተበዳሪው ሙሉ ስም የመያዣ ስጪው ስም ከተበዳሪው የሚፈለግበት ቀሪ ዕዳ የንብረቱ ዓይነትና አገልግሎት የቦታው ስፋት የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ ቁጥር ንብረቱ የሚገኝበት አድራሻ የጨረታ መነሻ ዋጋ በብር ጨረታው የሚካሄድበት ቀን የምዝገባ ሰዓት የጨረታ ሰዓት ጨረታው የወጣበት ጊዜ 1 አቶ በላይ ዳምጤ ተሾመ ተበዳሪው እስከ መጋቢት 09 ቀን 2018 ዓ.ም ብር 10,859,379.40 መኖሪያ ቤት 435 ካ.ሜ 46378/2014 ባህር ዳ ከተማ ጣና/ክ/ ከተማ ቀበሌ 16 20,667,474.00 ሚያዝያ 19 ቀን 2018 ዓ.ም 4:00-5:30 5:30-6:00 ለመጀመሪያ ጊዜ 2 ያሬንጃ የታሸጉ መጠጦች ጅምላ ንግድ ኃ/የተ/የግ/ማህር አቶ ተፈራ አላምራው ታዬ እስከ መጋቢት 09 ቀን 2018 ዓ.ም ብር 8,727,283.33 መኖሪያ ቤት 280 በቀድሞ 26085/2002 በአዲሱ የቁ/መ/ል/መለያ ኮድ AM00101041400 6 ባህር ዳር ከተማ አጼ/ቴዎድሮስ ክ/ከተማ ቀበሌ 11 26,915,670.48 ሚያዝያ 20 ቀን 2018 ዓ.ም 4፡00 5፡30-6፡00 ለመጀመሪያ ጊዜ 3 አቶ ይከበር ሞላ ሲሳይ ተበዳሪው እስከ መጋቢት 09 ቀን 2018 ዓ.ም ብር 12,624,837.22 መኖሪያ ቤት 200 በቀድሞ 32157/07 በአዲሱ የቁ/መ/ል/መለያ ኮድ AM00105410201 1 ባህር ዳር ከተማ ዳ/ም ክ/ከተማ፣ ቀበሌ ሰላም 13,142,404.18 ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም 4፡00 5፡30-6፡00 ለመጀመሪያ ጊዜ በመሆኑም ተጫራቾች ለጨረታ ከመቅረባቸው በፊት የሚከተሉትን ደንቦች መገንዘብ ይኖርባቸዋል፡: ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ንብረት የጨረታ መነሻ ዋጋውን ¼ (አንድ አራተኛ) በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይም ሲ.ፒ.ኦ በአቢሲንያ ባንክ (አ.ማ) ስም በማሰራት ለጨረታ ማስከበሪያ በማስያዝ በጨረታው ለመሳተፍ ይችላሉ፡፡ የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ ከባንኩ በደብዳቤ ከተገለጸለት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ በ15 (አስራ አምስት) ቀናት ውስጥ አጠቃሎ ከፍሎ በጨረታ ያሸነፈበትን ንብረት/ንብረቶች መረከብ ይኖርበታል፡፡ በእነዚህ ቀናት ውስጥ ካልከፈለ ጨረታው ተሰርዞ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል፡፡ በጨረታው ለተሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ሲ.ፒ.ኦ ወዲያውኑ ይመለስላቸዋል፡፡ ተበዳሪው/መያዣ ሰጪው በሐራጁ ቀንና ሰዓት በቦታው መገኘት ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ባይገኙ ሐራጁ በሌሉበት ይካሄዳል፡፡ የጨረታው አሸናፊ ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያያዙ ማናቸውም ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎችን ፣ እንዲሁም ከስም ዝውውር ጋር የሚገናኙ ማናቸውም ወጪዎችንም ገዢ ይከፍላል፡፡ ውዝፍ የሊዝ ክፍያ ካለ ባንኩ የሚከፍል ሲሆን ቀሪ የሊዝ ክፍያ ገዢ ከሚመለከተው የመንግስት አካል ጋር ይዋዋላል፡፡ ንብረቶቹን በሥራ ሰዓት ፕሮግራም አሲዞ ለመጎብኘት ወይም ለማየት ይቻላል፡፡ በባንኩ ብድር ፖሊሲ እና መመሪያ መሠረት መስፈርቱን ለሚያሟሉ የጨረታው ከፍተኛ ዋጋ አቅራቢዎች ባንኩ ከፊል ብድር ሊሰጥ ይችላል፡፡ የጨረታው የሚከናወነው ንብረቶቹ በሚገኙበት ስፍራ ነው፡፡ ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 058-320-96-60/ ወይም 09- 53-84-70-04 ባህር ዳር በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡፡ ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
Closing Date
Check Details
ወጋገን ባንክ አ.ማ በአዋጅ ቁጥር 97/90 እና 216/92 መሰረት ከዚህ በታች የቀረበውን የመያዣ ንብረት በግልጽ የሐራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል
ወጋገን ባንክ አ.ማ ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የሐራጅ ማስታወቂያ ቁጥር፡ ወጋገን 017/2018 ወጋገን ባንክ አ.ማ በአዋጅ ቁጥር 97/90 እና 216/92 መሰረት ከዚህ በታች የቀረበውን የመያዣ ንብረት በግልጽ የሐራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል ተቁ የተበዳሪው ስም የንብረት አስያዥ ስም አበዳሪው ቅርንጫፍ የንብረቱ አድራሻ የቦታው ስፋት የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ ቁጥር የንብረቱ ዓይነት/የይዞታው አገልግሎት የጨረታ መነሻ ዋጋ ጨረታው የሚከናወንበት ቀን ከተማ/ ክልል ክ/ከተማ/ ከተማ/ዞን ወረዳ /ቀበሌ 1 አቢሲንያ የቄራ አገልግሎት ኃ/የተ/ የግ/ማህበር አቶ ቴዎድሮስ ታደሰ በቅሎቤት አዲስ አበባ የካ 13 500 ካ/ሜትር AA000051306364 መኖሪያ ቤት (G+2) 30,627,626.14 ሚያዝያ13 ቀን 2018 ዓ.ም ከጧቱ 3፡00 – 6፡00 ሰዓት ማሳሰቢያ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው የጨረታ መነሻ ዋጋ ¼ (አንድ አራተኛ) በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ሰነድ (C.P.O) በወጋገን ባንክ አ.ማ ስም በማሰራት በጨረታው ዕለት በመቅረብና በመመዝገብ በጨረታው ላይ መሳተፍ ይችላሉ፡፡ የጨረታ አሸናፊ ከባንኩ የብድር ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ማሸነፉን የሚገልጽ ደብዳቤ ከተሰጠው ቀን ጀምሮ ቀሪውን ገንዘብ በ15 /አስራ አምስት/ ቀናት ውስጥ አጠናቆ መክፈል ይኖርበታል፡፡ ባይከፍል ግን የሐራጁ ውጤት ተሰርዞ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል፣ ላላሸነፉት ተጫራቾች ግን ያስያዙት ሲፒኦ ወዲያዉኑ ይመለስላቸዋል፡፡ ጨረታውን ላሸነፈ፤ የባንኩን የብድር ፖሊሲ፤ መመሪያ እና ቅድመ ሁኔታ ለሚያሟላ እንዲሁም ተጨማሪ የመያዣ ንብረት ለሚያቀርብ ተጫራች፤ ባንኩ በብድር መመሪያ መሰረት ብድር ሊያመቻች ይችላል፡፡ የተጫራቾች የምዝገባ ሰዓት፤ ከጧቱ 3፡00 – 4፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ ሲሆን ምዝገባው ከተጠናቀቀ በኋላ ለንብረቱ የሚመደበው የጥሪ ሰዓት 30 ደቂቃ ብቻ ነው፡፡ ሆኖም የጨረታው መጠናቀቂያ ሰዓት ድረስ አሸናፊው ካልተለየ አሸናፊ እስኪለይ ድረስ ጨረታው ይቀጥላል፡፡ በጨረታው የተሻለ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች ጨረታውን ካካሄደው ከባንኩ የብድር ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ማሸነፉን የሚገልጽ ደብዳቤ ሲደርሰው ብቻ አሸናፊ ይባላል፡፡ ንብረቱ በገዢው ስም እንዲዞር ባንኩ ለሚመለከተው መንግስታዊ አካል ደብዳቤ ይጽፋል፡፡ ጨረታው የሚካሄደው በወጋገን ባንክ ዋና መስርያ ቤት ህንጻ 13ኛ ወለል ላይ በሚገኘው የመሰብሰብያ አዳራሽ ይሆናል፡፡ ለሀራጅ ጨረታ የቀረበውን ንብረት ለመጎብኘት የሚፈልግ ተጫራች የጨረታው ቀን ከመድረሱ በፊት ከባንኩ ጋር ቀጠሮ በማስያዝ መጎብኘት ይችላል፡፡ ተበዳሪው /ንብረት አስያዥ/ ወይም ሁለቱም በጨረታው ቀን እና ሰዓት በቦታው ላይ መገኘት ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ተበዳሪው /ንብረት አስያዡ/ በጨረታ ቀን እና ሰዓት በቦታው ባይገኝ ጨረታው በሌለበት ይካሄዳል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ጨረታው ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች ወይም የተጫራቾች ህጋዊ ተወካዮች ብቻ ናቸው፡፡ ማንኛውንም ለመንግስት ሊከፈል የሚገባውን ክፍያ ተጨማሪ እሴት ታክስን ጨምሮ ሙሉ በሙሉ የጨረታው አሸናፊ የሚከፍል ይሆናል፡፡ ለበለጠ ማብራሪያ ወይም የጉብኝት ቀጠሮ ለማመቻቸት ወጋገን ባንክ አ.ማ የብድር ማስመለስ ዳይሬክቶሬት 011-558-18-37፣ መደወል ይችላሉ፡፡ ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ በጨረታው አይገደድም፡፡ ወጋገን ባንክ አ.ማ
Closing Date
Check Details
የኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ ሲገለገልባቸው የነበሩ ያገለገሉ የተለያዩ አቅም ያላቸው ጀነሬተሮች፣ ካዝናዎች፣ኮምፒውተሮች፣ ፕሪንተሮች፣ ዩፒኤሶች ፣ የብር መቁጠሪያ ማሽኖች፣ የተለያዩ የቢሮ ወንበሮች (የመሽ ወንፊት፣ የፋቢሪክ እና የቆዳ)፣ ጠረጴዛዎች፣ የብረት ፋይል ካቢኔቶች፣ ካዉንተር እና ኬጂ፣ ያገለገሉ የመኪና ባትሪዎች፣ ያገለገሉ የመኪና ጎማዎች፣ አሮጌ ጋዜጣዎች፣ ባዶ የቶነር እቃዎች እና የ
የጨረታ ማስታወቂያ (ቁጥር FA- 07/2025/26) የዕቃዎቹ ዓይነትና ዝርዝር በጨረታው ሰነድ ላይ የሚገኝ በመሆኑ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት እስከ መጋቢት 7 ቀን 2018 ዓ.ም 8፡00 ሰዓት ድረስ የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርተፊኬት ወይም የግብር መለያ ካርድ ያላችሁ ተጫራቾች ቦሌ መንገድ የኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ ኢጆ ቅርንጫፍ ወይም በአቅራቢያዎ በሚገኝ የባንኩ ቅርንጫፍ በመሄድ ላገለገሉ ዕቃዎች ጨረታ ሰነድ መግዣ ብር 300.00 (ሦስት መቶ) በሂሳብ ቁጥር ETB1446500010001 በማስገባት ደረሰኙን በመያዝ የጨረታ ሰነዱን ቦሌ መንገድ ከአፍሪካ ኢንሹራንስ ፊትለፊት፣ ራንግ ህንጻ 7ኛ ፎቅ ከባንኩ ንብረት አስተዳደር ዋና ክፍል መውሰድ ይችላሉ። የዕቃዎቹን ዓይነትና ዝርዝር ሁኔታ በአካል ማየት ለሚፈልጉ ተጫራቾች የከፈሉበትን ስሊፕ እና የጨረታ ሰነዱን በመያዝ ሱሉልታ አካባቢ ሁለት ቦታ በሚገኙት የባንኩ መጋዘኖች ሹፉኔ ቻይና ጋራጅ 100 ሜትር ገባ ብሎ አነን ሰላሌ የወተት ማቀነባበሪያ ቅጥር ግቢ ውስጥ እና ሱሉልታ አዲስ የተሰራዉ ክ/ከተማ ከዋና መንገዱ ወደ ቀኝ 200 ሜትር ገባ ብሎ በሚገኘው ፒልከን ተብሎ በሚታወቀው የባንኩ ግምጃ ቤት ውስጥ በመገኘት ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታ ሰነዱን የገዙ ተጫራቾች ብቻ በተቀመጠው ፕሮግራም መሠረት የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ፣ መጋቢት 2 እና መጋቢት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ከጧቱ 3፡00 ሰዓት እስከ 10፡00 ሰዓት ድረስ እንዲሁም መጋቢት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ከጧት 3፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት መጎብኘት ይችላሉ። ገዢዎች የሚገዙበትን ዋጋ በታሸገ ኤንቬሎፕ እስከ ጨረታ መዝጊያ መጋቢት 7 ቀን 2018 ዓ.ም 8፡00 ሰዓት ድረስ ቦሌ መንገድ ራንግ ህንጻ ንብረት አስተዳደር ዋና ክፍል በአካል ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸውን በመላክ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ በማስገባት መጫረት ይችላሉ። ባንኩ የሚከተለው የማወዳደሪያ ዘዴ በሰነዱ ሰንጠረዥ ላይ ንብረቶቹ እንደተዘረዘሩት ዓይነት በተናጠል መስመር በመስመር ሲሆን ባንኩ የተሻለ ሆኖ ካገኘም በጥቅል ወይም በጅምላ ያወዳድራል። ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ንብረት የጠቅላላ መነሻ ዋጋ 10% (አስር በመቶ)ዉን በባንክ ክፍያ ማዘዣ (CPO) የጨረታ ማስከበሪያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፤ በተጨማሪም የጨረታ መነሻ ዋጋ ለሌላቸው የሚገዙበትን ጠቅላላ ዋጋ 10% ማስያዝ ይኖርባቸዋል። ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) 15% በተጨማሪነት መኖር አለመኖሩን በግልፅ በሰነዱ ላይ በፅሁፍ መግለፅ ይኖርባችዋል። የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ሳይያያዝ የሚቀርብ የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም። አሸናፊ መሆናቸው የተገለፀላቸው ተጫራቾች ያሸነፉትን ንብረት ሙሉ ክፍያውን በአምስት ቀናት ውስጥ ከፍለው ማንሳት ይኖርባቸዋል፤ ካልሆነ ግን ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ሲፖኦ ውርስ ይደረጋል። ጨረታው ሰኞ መጋቢት 7 ቀን 2018 ዓ.ም በ 8፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዛው ዕለት ሰኞ መጋቢት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ላይ ራንግ ህንጻ 7ኛ ፎቅ የስብሰባ አዳራሽ ውስጥ ተጫራቾች በተገኙበት የጨረታ ሰነዱ የሚከፈት መሆኑን እንገልፃለን። ባንኩ የተሸለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ (አ.ማ) ስልክ ቁጥር 0115576174 ፖ.ሣ.ቁ 16936 ማህበረሰቡን ማጎልበት፣ ህይወትን መለወጥ!
Closing Date
Check Details
የኢትዮጵያ ጠለፋ መድን አ.ማ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ያገለገሉ እቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
የኢትዮጵያ ጠለፋ መድን አ.ማ የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር፡ኢጠመ/0005/2018 ያገለገሉ የተለያዩ እቃዎችን ለመሸጥ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ ኩባንያችን የኢትዮጵያ ጠለፋ መድን አ.ማ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ያገለገሉ እቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ ተ.ቁ የዕቃዎች ስም ዝርዝር ምርመራ 1 የተለያዩ የቢሮ ተሽከርካሪ ወንበሮች የዕቃዎች ብዛትና መጠን በጨረታ ሰነድ ውስጥ በዝርዝር ተጠቅሰዋል 2 የቢሮ ጠረጴዛ 3 ኪችን ካብኔት 4 የኪችን ወንበሮች 5 የመስታወት መጋረጃ 6 የተለያዩ የቀላል መኪና ጎማዎችና መለዋወጫዎች 7 UPS ባትሪዎች 8 የተለያየ ብዛት እና መጠን ያላቸው የኤጋ ቆርቆሮዎች 9 ትራንስፓረንት ቆርቆሮዎች 10 መስታወቶች 11 ጣውላዎች 12 ፕላስቲክ የበር ፍሬሞች 13 ኮንዲት 14 አንጉላር ብረት 15 አልሙኒየም ክላዲንግ 16 የመስኮት አልሙኒየም ክላዲንግ ፍሬም 17 ቶነር ካርትሬጅ 18 ልዩልዩ እቃዎች በዚሁ መሠረት በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም ግለሰብ ወይም ድርጅት የሚሸጡትን እቃዎች ልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 9 ጆሳንሰን አካባቢ በሚገኘው የድርጅቱ ህንፃ 7ኛ ፎቅ በመምጣት የሚሸጡትን እቃዎች ዝርዝር የያዘ ሰነድ ከመጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ባሉት አስር (10) የሥራ ቀናት በስራ ሰዓት በመገኘት ማየት እና ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ፡፡ ሰለሆነም ፍላጎት ያላችሁ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርቶች እና ሰነዶች በማሟላት እንድትወዳደሩ እንጋብዛለን፡- ተጫራቾች የታደሰ ህጋዊ የንግድ ሥራ ፈቃድ፤ የንግድ ምዝገባ ፈቃድ፤ የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ምስክር ወረቀት፤ የግብር ከፋይ ምዝገባ ምስክር ወረቀት እና የመሳሰሉትን ሰነዶች በማያያዝ ማቅረብ አለባችሁ፡፡ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋት 2፡00 እስከ 11፡00 ሰዓት ባለዉ ጊዜ ዉስጥ ለሽያጭ የቀረቡትን እቃዎች ልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 09 ጆሳንሰን አካባቢ በሚገኘው የድርጅቱ ህንፃ 7ኛ ፎቅ በአካል በመምጣት መመልከት ትችላላችሁ፡፡ ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት እቃዎች ለሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ 10 ፕርሰንት የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ከጨረታ ሰነድ ጋር በማያያዝ በታሸገ ኤንቨሎፕ ለዚሁ በተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ዉስጥ ጨረታዉ ከመዘጋቱ በፊት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታዉ መገምገሚያ መስፈርት ዋጋዉ፤ የተሟላ ጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና(ሲፒኦ) እንዲሁም በሰነዱ የተገለጹትን ዶክመንቶች አሟልቶ መገኘት ነዉ፡፡ ከላይ በተራ ቁጥር 4 የተገለጸዉን የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ያላስያዘ እና የተዘረዘሩትን ሌሎች ነጥቦች ያላሟላ ተጫራች ከጨረታዉ ዉድቅ ይደረጋል፡፡ የጨረታ ሳጥኑ ጨረታዉ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን በ10ኛዉ ቀን ማለትም አርብ መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚያኑ ቀን በ8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በኩባንያዉ መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ ተጫራቹ በራሱ ዉሳኔ ጨረታዉ በሚከፈትበት ጊዜ ሳያገኝ ቢቀር የጨረታዉን መከፈት አያስተጓጉልም፡፡ በጨረታዉ አሸናፊ ተጫራቾች ጨረታዉን ማሸነፋቸዉ ከተነገረበት ወይም የስማቸዉ ዝርዝር በማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ ከተለጠፈበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር ከ2 /ሁለት/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ዉስጥ የዉል ማስከበሪያ የዉል ዋጋዉን 10 በመቶ በማቅረብ ኩባንያዉ ጋር ዉል መፈራረምና ያሸነፉበትን ዋጋ ሙሉ መክፈል ይኖርባችዋል፡፡ ሆኖም ከላይ በተገለጸዉ መሰረት ዉል ካልፈረሙ ወይም ሙሉ ክ
Closing Date
Check Details
International Committee of the Red Cross ICRC, LIST OF USED VEHICLES AND GENERATORS FOR SALE
International Committee of the Red Cross ICRC Ethiopian Delegation Logistics Unit /Addis Ababa Bole Sub City Kebele 12/13 Around Agricultural Research Institute or Egziabher Ab Chruch Tel.: +251 011 647 83 00 Email: add_logistics_services@icrc.org LIST OF USED VEHICLES AND GENERATORS FOR SALE Lot No. & Description Code Model Type/Name Year of Production Mileage KM/HR Lot No. 01 – PEUGEOT_ RIFTER _ EC9HPA_ 1.6_DL_M/T_4x2, DL 22447 EC9HPA 15.04.2019 67 970 Lot No. 02 – TOYOTA LC HARDTOP HZJ76L-RKMRS (Accidented / Damaged) 17510 HZJ76L-RKMRS 01.03.2019 92 346 Lot No. 03 – RENAULT TRUCK KERAX 330.19 4X4 30987 KERAX 330.19 4X4 MD 01.06.2013 250 250 Lot No. 04 – RENAULT TRUCK KERAX 440.34 6X4 30988 KERAX 440.34 6X4 HD 01.06.2013 287 325 Lot No. 05 – DOLL 3 AXLE DRAW BAR TRAILER 40391 TRAILER 01.06.2013 N/A Lot No. 06 – ZORDAN GENERATOR LMDE 22PM0 22 KVA _DL 84696 LMDE 22PM0 01.02.2021 55 Lot No. 07 – ZORDAN GENERATOR LMDE 22PM0 22 KVA_DL 84723 LMDE 22PM0 01.03.2021 2 Lot No. 08 – ZORDAN GENERATOR LMDE 15PM0 15 KVA _DL 84762 LMDE 15PM0 01.07.2021 402 Lot No. 09 – ZORDAN GENERATOR LMDE 15PM0 15 KVA _DL 84763 LMDE 15PM0 01.07.2021 555 Lot No. 10 – ZORDAN GENERATOR LMDE 15PMO 15 KVA_DL 84497 LMDE 15PM0 01.01.2019 1112 Lot No. 11 – ZORDAN GENERATOR LMDE 15PMO 15 KVA_DL 84554 LMDE 15PM0 01.01.2020 2437 Lot No. 12 – ZORDAN GENERATOR LMDE 15PMO 15 KVA_DL 84691 LMDE 15PM0 01 02 2021 141 Lot No. 13 – ZORDAN GENERATOR LMDE 15PMO 15 KVA_DL 84721 LMDE 15PM0 01.03.2021 130 ATTENTION!!! ALL ASSETS ANNOUNCED FOR SALE ARE TAX & DUTY UNPAID Conditions and Procedures: All vehicles are sold in their present condition (“as is & where is”) on the basis of no guarantee or warranty given in condition of usability. Lots cannot be divided or combined, and price should be submitted for each lot separately. The auction winner or buyer will be responsible to pay taxes, customs duties and other charges of public nature levied by the government and must be paid to the government when assessed (except for Organizations or Companies with duty-free privileges, which must obtain the required duty-free customs clearance for the purchased items and submit the relevant documentation prior to collection). ICRC bears no responsibility for these charges in any manner. All Lots can be viewed during working hours from Monday 23rd of March to Monday 30th of March 2026, 12:00 PM at ICRC Logistic Compound Unit located along Egziabher Ab to Meta Road around KAKI Trading next to UNICEF Warehouse. Everybody interested in bidding for the vehicles and generators, shall submit his/her offer in a sealed Envelope marked “Confidential & Lot N°xx” before Tuesday 31st of March 2026 12:00 PM at ICRC logistic Unit (see on the top). The opening of the bids is not public, it will take place at the ICRC Logistics office within ten working days after the auction closing date. ICRC Delegation in Ethiopia has the right to reject any or all bids without explaining the reason. Each bidder must deposit 10% of his/her offer amount, by the name of International Committee of The Red Cross as a bid bond by CPO cheque (Only CPOs issued by Commercial Bank of Ethiopia (CBE) is accepted), which will be deducted from the sales price if the bidder becomes successful. Within 15 days of auction result announcement, the winner should process the final payment & sign a sales agreement. Tax and duties must be processed within 15 days after name transfer permit letter is issued to Customs Office by Ministry of Foreign Affair MoFA. Asset handing over will be done only upon submission of custom declaration document. The bid bond will not be refunded if the auction winner doesn’t fulfill all the mentioned conditions or refuses to make the final payment (it will result in forfeiture of the bid bond deposit). The bid bond CPO of the non-winners will be refunded within five days after the announcement of the auction result. Anybody who does not agree with the above-mentioned conditions and procedures shall not bid.
Closing Date
Check Details
Nib International Bank would like to invite interested and eligible bidders for the procurements of different goods & services through open tender.
Invitation to National Competitive Bid For the procurement of different goods and services Nib International Bank would like to invite interested and eligible bidders for the procurements of different goods & services through open tender. S. N Description Of Goods/Services BID REF.NO Bid Bond Amount Bid closing Bid opening 1. Procurements of different RAM & Hard Disc NIB/57/2025/26 100,000.00 March 26, 2026 At 03:00 PM March 26, 2026 At 03:15 PM 2. Procurement of Vehicle GPS Subscription Services NIB/34/2025/26 (Re-bid) 50,000.00 March 17, 2026 At 03:00 PM March 17, 2026 At 03:15 PM 3. Procurement of different garaje materials NIB/58/2025/26 50,000.00 March 31, 2026 At 03:00 PM March 31, 2026 At 03:15 PM Bidding will be conducted in accordance with the open tendering procedure contained in the procurement manual of the Bank. A complete set of bidding documents may be purchased by interested bidders upon payment of a non-refundable fee of birr 200.00 (Birr Two Hundred) for each lot bid documents by using account number ETB 1764600010001 starting from March 11, 2026 during office hours from Monday to Friday: 8:00 am – 12:00 am and 1:00 pm -5:00 Pm and Saturday: 8:00 am – 12:00 am. From the address mentioned below. Address: Nib International Bank Head Office 26th floor, located at Senga Tera area, Procurement Division for further information: Telephone +251 11 5 512650/+251 11 5 580651, Fax +251 11 5 622448. For eligibility, bidders should bring copy of renewed Trade license, certificate of registration, Tax payers registration certificate, Value added tax certificate and tax clearance certificate. Bid proposal must be sealed and deposited in the tender box prepared for this purpose during office hours at the address mentioned under serial number 3 before the bid closing time. Bid proposal must be accompanied in the form of CPO or unconditional bank guarantee valid for not less than 90 days from the date of bid opening. This bid will be opened on the presence of bidders or their representatives who choose to attend at the address mentioned under serial number 3. Bidders are advised to review the bid document carefully before submitting their bids and failure to observe the instructions and conditions in the bidding document will constitute grounds for rejection. The Bank reserves the right to reject the bid either partially or fully without giving reasons thereof. NIB International Bank Telephone +251 11 5 512650/+251 11 5580651 Fax +251 11 5 622448 Addis Ababa, Ethiopia
Closing Date
Check Details
ብርሃን ኢንሹራንስ አ.ማ የካሣ ክፍያ ፈጽሞ የተረከባቸውን ከባድና ቀላል የተጎዱ ተሽከርካሪዎች ፣የተሽከርካሪዎች መለዋወጫ (ፕላስቲክ ነክ የሆኑና ያልሆኑ ፣ራዲያተር ፣ባምፐር፣ ባትሪ ፣ቸርኬ፣ ጎማ ፣የተለያዩ ገቢናዎች ፣ኮንቴነር ፣የተለያዩ መብራቶች ወዘተ…) እንዲሁም ኩባንያው ሲገለገልባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎች ከዚህ በታች ባለው ዝርዝር መሰረት ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡
የጨረታ ማስታወቂያ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 00 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ዘወትር በስራ ሰዓት ጨረታው እስከሚያበቃበት ቀን ድረስ ከዋናው መስሪያ ቤት መግዛት ይችላሉ፡፡ ንብረቶቹን ባሉበት ሁኔታ በብርሃን ኢንሹራንስ አ.ማ የተጎዱ ንብረቶች ማከማቻ ቦታ አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወረዳ 7 ልዩ ቦታው ቃሊቲ 4ዐ/60 ኮንደሚኒየም በኩል ገባ ብሎ በተለምዶ የቆላ ዝንብ አካባቢ (ጨሬ ሰፈር) የጨረታ ሰነድ የገዙበትን ደረሰኝ በመያዝ ንብረቶቹን መመልከት ይችላሉ፡፡ በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ለመጫረት የሚፈልገውን የንብረት ዓይነት እና ያቀረበውን የጨረታ ዋጋ ዝርዝር በመግለጽ ፤የጨረታ ማስከበሪያ የንብረቱን የጨረታ መነሻ ዋጋ 15 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ ሲ.ፒ.ኦ. በብርሃን ኢንሹራንስ አ.ማ. ስም በማስያዝ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ መጋቢት 18 ቀን 2ዐ18 ዓ.ም. ድረስ በሥራ ቀናት ብርሃን ኢንሹራንስ አ.ማ. ዋናው መ/ቤት ቂርቆስ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 03 ቦሌ ወሎ ሰፈር ጋራድ ሲቲ ሴንተር 7ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 7 በአካል በመገኘት የጨረታ ሰነዱን በሰም በታሸገ ፓስታ ለሚጫረቱበት የዕቃ አይነት ማስገባት ይችላሉ፡፡ በጨረታ ለተሸነፉ ያስያዙት ሲ.ፒ.ኦ. ይመለስላቸዋል፡፡ ለጨረታ አሸናፊዎች ደግሞ ያዝያዙት ገንዘብ ለሚገዙት ተሽከርካሪ ወይም መለዋወጫ ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር ይታሰብላቸዋል፡፡ አሸናፊዎች በጨረታው ላሸነፉት ንብረት ቀሪውን ክፍያ እና 15% የተጨማሪ እሴት ታክስ አክለው በመክፍል የጨረታው ውጤት ከተገለጸበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት 5 የስራ ቀናት ውስጥ እቃዎችን መረከብ ይኖርባቸዋል፡፡ በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ያሸነፉትን ንብረት ከፍለው ካልወሰዱ ኩባንያው ለጨረታ ያስያዙትን ሲፒኦ ገቢ አድርጎ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ የተጨማሪ እሴት ታክስን የሚያጠቃልል መሆኑን በግልጽ ሁኔታ በሚያቀርቡት የጨረታ ሰነድ ላይ ካልተገለጸ በስተቀር በቀረበው ዋጋ ላይ 15% ተጨማሪ እሴት ታክስን ተጨምሮ የሚታሰብ ይሆናል፡፡ ተሽከርካሪዎች በጨረታ እስከተሸጡበት ጊዜ ድረስ የሚፈለግ ግብርና ታክስ ወይም ሌላ ክፍያ የሻጩ ኃላፊነት ይሆናል፡፡ አሸናፊ ተጫራቾች የገዙትን ዕቃ ከሪከቨሪ በራሳቸው ወጪ አስነስተው ይወስዳሉ፡፡ ጨረታው መጋቢት 18 ቀን 2ዐ18 ዓ.ም. ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን በ 8፡3ዐ ሰዓት ላይ የሚከፈት ሲሆን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው ይከፈታል፡፡ ኩባንያው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0114-67-44-23/46 ወይም 0114-70-40-54 መደወል ይቻላል፡፡
Closing Date
Check Details
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአዋጅ ቁጥር 97/90 እና 216/92 በተሰጠው ስልጣን መሰረት ቀጥሎ የተመለከቱትን ንብረቶች ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ሐራጅ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
የሐራጅ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአዋጅ ቁጥር 97/90 እና 216/92 በተሰጠው ስልጣን መሰረት ቀጥሎ የተመለከቱትን ንብረቶች ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ሐራጅ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ ተ.ቁ የተበዳሪው ስም የንብረት አስያዥ ስም የመያዣ ንብረቱ መለያ የሐራጅ መነሻ ዋጋ (ብር) ሐራጁ የሚከናወንበት ቀን እና ሰዓት አድራሻ የይዞታ ማረጋገጫ ሰነድ ቁጥር/መለያ የይዞታው ስፋት (ካ.ሜ) የይዞታው አይነት/የሚሰጠው አገልግሎት 1. ሚድ ትሬዲንግ ሼር ካምፓኒ ተክሌ ደስታ አዲስ አበባ ቦሌ ክ/ከ/ወረዳ 06 AA000060601983 224 ለመኖሪያ ቤት 23,211,140.65 16/08/2018 ዓ.ም 3፡00- 4፡00 ጠዋት 2. አቶ መስፍን ባዘዘው ጂቲኤም ንግድ አ.ማ አዲስ አበባ ከተማ ለሚኩራ ክ/ከ AA000060809292 933 በግንባታ ላይ የሚገኝ ለንግድ አገልግሎት የሚውል ህንፃ 461,950,785.14 16/08/2018 ዓ.ም 4፡00- 5፡00 ጠዋት 3. አቶ አሰፋ ዱካሌ ሻሸሞ ዱካሌ ዋቀዮ ሐዋሳ ከተማ መናኸሪያ ክ/ከተማ በቀድሞ 5208፣ በአዲሱ SN001010806078 750 ለድርጅት 10,813,576.57 16/08/2018 ዓ.ም 5፡00 – 6፡00 ጠዋት 4. ዱካሌ እና ቤተሰቦቹ ቡና መፈልፈያ እና ማጠቢያ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ሃሪፋ ጠ/ን/ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ሃዋሳ ከተማ፣ ሐይቅ ዳር ቀበሌ 14039 1501.5 ለንግድ ዓላማ የሚውል ሕንጻ 53,445,074.50 16/08/2018 ዓ.ም 8፡00- 9፡00 ከሰዓት 5. መሃመድ ሴሮ ተበዳሪዉ ሻሸመኔ ከተማ አዋሾ ቀበሌ 3509 500 ለመኖሪያ ቤት 3,986,617.18 16/08/2018 ዓ.ም 3፡00- 4፡00 ጠዋት 6. መሃመድ ሴሮ ተበዳሪዉ ሻሸመኔ ከተማ አዋሾ ድንቁ ክ/ከተማ 5907 1,185 ለመኖሪያ ቤት 9,555,850.08 16/08/2018 ዓ.ም 4፡00- 5፡00 ጠዋት 7. አሌክሳንድራ ታደሰ ባዶ ተበዳሪዉ ሃዋሳ ከተማ፣ ታቡር ክ/ከተማ ሂማታ ቀበሌ 8580 150 ለመኖሪያ ቤት 2,724,365.26 16/08/2018 ዓ.ም 3፡00- 4፡00 ጠዋት በመሆኑም፡- ማንኛውም ተጫራች ወይም ህጋዊ ወኪሉ የሐራጁን መነሻ ዋጋ 1/4 ኛ በተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ (ሲፒኦ) በማስያዝ መጫረት ይችላል፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲፒኦ ማቅረብ ተመራጭ ነው፡፡ ከተ.ቁ 1-4 የተዘረዘሩ ንብረቶች ጨረታ የሚከናወነው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዲሱ ዋናው መስሪያ ቤት 42ኛ (ወለል) ፎቅ ቢሮ ቁጥር 4203 ነው፤ በተራ ቁጥር 5-6 ላይ የተጠቀሰው ንብረት ሻሸመኔ ዲስትሪክት ቅጥር ግቢ ሲሆን በተራ ቁጥር 7 ላይ የተጠቀሰው ንብረት ሀዋሳ ዲስትሪክት ቅጥር ግቢ ነው፡፡ የንግድ ማህበርን ወክሎ ለመጫረት የማህበሩን መመስረቻ እና መተዳደርያ ደንብ የያዘና በማህበሩ ስም ንብረት ለመግዛት ስልጣን ያለው መሆን ያለበት ሲሆን ይህንኑ የሚያረጋግጥ ሰነድ በማቅረብ ይሆናል፡፡ ለጨረታ ከቀረቡ ከመኖሪያ ቤቶች ዉጪ የሆኑ ንብረቶችን በጨረታ አሸንፎ የገዛ በሽያጩ ገንዘብ ላይ 15% ተጨማሪ እሴት ታክስ ይከፍላል፡፡ የጨረታ አሸናፊ ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያያዙ ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎች፣ ግብር፣ እንዲሁም ከስም ዝውውር ጋር የሚገናኙ ማናቸውንም ወጪዎች ይከፍላል፡፡ ንብረቶቹን ለመጎብኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋናው መስሪያ ቤት 42 ፎቅ በአካል በመቅረብ ባንኩ በሚያመቻቸው ፕሮግራም መሰረት መጎብኘት ይቻላል፡፡ በጨረታው ከፍተኛ የሆነ የጨረታ ዋጋ የሰጠ ተጫራች በባንኩ የጨረታ አሸናፊነት ደብዳቤ ከደረሰው ቀን ጀምሮ ቀሪ የሽያጩን ገንዘብ በ15 ቀናት ውስጥ አጠቃሎ መክፈል ያለበት ሲሆን ክፍያውን በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ካልከፈለ ለሐራጁ ማስከበሪያ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል፡፡ ንብረቶቹን በጨረታ አሸንፎ የገዛ ግለሰብ/ድርጅት የሽያጭ ገንዘቡን ከፍሎ ባጠናቀቀ በ15 ቀናት ጊዜ ውስጥ ንብረቱን መረከብ ያለበት ሲሆን በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ንብረቱን ካልተረከበ በንብረቱ ላይ ለሚደርስ ጉዳት ባንኩ ኃላፊነት
Closing Date
Check Details
አዲስ ባንክ አ.ማ ለሰጠዉ ብድር በዋስትና የያዘዉን ተሸከርካሪ በአዋጅ ቁጥር 1147/2011 በተሰጠዉ ስልጣን መሰረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የሐራጅ ማስታወቂያ አዲስ ባንክ አ.ማ ለሰጠዉ ብድር በዋስትና የያዘዉን ተሸከርካሪ በአዋጅ ቁጥር 1147/2011 በተሰጠዉ ስልጣን መሰረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ በዚሁ መሰረት ማንኛዉም ተጫራች ሐራጁ በሚካሄድበት ቀን ንብረቱ በሚገኝበት ቦታ በመገኘት በጨረታዉ ተወዳድሮ ንብረቱን እንዲገዛ ተጋብዟል፡፡ የተበዳሪዉ ስም የንብረት አስያዥ ስም አበዳሪው ቅርንጫፍ ለጨረታ የቀረበዉ የመያዣ ንብረት አይነት እና ሞዴል የሰሌዳ ቁጥር የሞተር ቁጥር የሻንሲ ቁጥር የጨረታዉ መነሻ ዋጋ ጨረታዉ የሚከናወንበት ቦታ ጨረታዉ የሚከናወንበት ቀንና ሰዓት ግሪን ላንድ ኃ/የተ/የግ/ማህበር አቶ ዳሪዮ ሞሬሎ አብይ ቅርንጫፍ ተሸከርካሪ-ላንድ ክሩዘር (ሀርድ ቶፕ) ጃፓን ሰራሽ ቶዮታ፤ማኑዋል የ09/2017 ምርት ኮድ 3-A53691 አ.አ 1HZ-0886065 JTEE71J 307039510 16,500,000 (አስራ ስድስት ሚሊየን አምስት መቶ ሺ ብር የባንኩ መኪና ማቆያ በሚገኝበት አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወረዳ 05 ቁስቋም ማርያም ቤተክርስቲያን ፍትለፊት ሚያዝያ 3 ቀን 2018 ዓ/ም ከጠዋቱ 4.00-6.00 ሰዓት ተጫራቾች የጨረታዉን መነሻ ዋጋ 25% በባንኩ የክፍያ ማዘዣ ሰነድ(cpo) አሰርቶ በጨረታዉ ቀን ጨረታው በሚካሄድበት ቦታ በመቅረብ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ፡፡ ጨረታዉ በማስታወቂያዉ ላይ በተጠቀሰዉ ቀንና ሰዓት ባለዕዳዎቹ ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸዉ፣ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸዉ፣ታዛቢዎች በተገኙበት፣የመያዣ ንብረቱ በሚገኝበት የሚካሄድ ይሆናል፡፡ ጨረታው እለት ተበዳሪዎቹ፤ አስያዥ ወይም ሕጋዊ ወኪሎቹ ባይገኘም ጨረታው የሚከናወን ይሆናል፡፡ የጨረታዉ አሸናፊ ያሸነፈበትን ዋጋ ጨረታዉ ከተከናወነበት ማግስት ጀምሮ በሚቆጠር 15 ቀን ዉስጥ ለባንኩ ገቢ ማድረግ ይኖርበታል፡፡ በእነዚህ ቀናት ዉስጥ ካልከፈለ ግን ለጨረታ ያስያዘዉ ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ጨረታዉ ተሰርዞ ለሐራጅ የሚቀርብ ይሆናል፡፡ በጨረታዉ ተሳትፈዉ ላላሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ጥሬ ገንዘብ ወይም ሲፒኦ ወዲያኑ ተመላሽ ይደረግላቸኋል፡፡ ኃ/የተ/የግል ማህበርን ወይም አክሲዮን ማህበርን ወክሎ መጫረት የሚፈልግ ሥራ አስኪያጅ ወይም ም/ሥራ አስኪያጅ የድርጅት የመመስረቻ ጽሑፍ ይዞ መቅረብ ያለበት ሲሆን የሥራ አስኪያጅ ወይም የም/ሥራ አስኪያጅ ለዉጥ ተደርጎ ከሆነ ይህንኑ የሚገልጽ በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽ/ቤት ቃለ ጉባኤ ከመመስረቻ ጽሑፍ ጋር ይዞ መቅረብ አለበት፡፡ የጨረታዉ አሸናፊ ለመንግስት የሚከፈለዉን አስፈላጊ ግብር እና ተጨማሪ እሴት ታክስ ክፍያ ይከፍላል፡፡ ተጫራቾች ለጨረታ የቀረበዉ ንብረት ያለበትን ሁኔታ በተመለከተ ከጨረታዉ ቀን በፊት ባሉ የስራ ቀናት እና ሰዓት በባንኩ አበዳሪ ቅርንጫፍ በመቅረብ በሚያዘጋጀዉ ፕሮግራም መሰረት ንብረቱ ያለበትን ሁኔታ መመልከት ይችላሉ፡፡ ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡ ለተጨማሪ መረጃ አዲስ ባንክ አ/ማ ሕግ አገልግሎት መምሪያ በስልክ ቁጥር 0115571934፣ አብይ ቅርንጫፍ 0118276004 በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡፡ አዲስ ባንክ አ.ማ
Closing Date
Check Details
The British Embassy in Addis Ababa is conducting a public auction for the disposal of various surplus items, including: Fuel Tank, 20ft Containers, Printer and Scanners, Generators, and other Scrap Materials.
British Embassy Addis Ababa – Public Auction Notice The British Embassy in Addis Ababa is conducting a public auction for the disposal of various surplus items, including: Fuel Tank, 20ft Containers, Printer and Scanners, Generators, and other Scrap Materials. Auction Details: Viewing & Bidding Date: 24 July 2025 | 9:00 AM – 4:00 PM Result Announcement: 28 July 2025 Item Collection: 30 – 31 July 2025 | 9:00 AM – 4:00 PM Location: British Embassy compound How to Participate: Register by 5:00 PM on 22 June 2025 through the following: Online: https://forms.cloud.microsoft/e/Ef8W057vt8 Bidding will be done via mobile phone using a QR code system. Requirements: Valid ID is required Participants must be legally eligible to bid External bidders must pay a non-refundable fee of 5,000 ETB in cash on viewing day to participate. External bidders are prohibited from parking inside or around the Embassy compound. Participants are responsible for arranging suitable parking outside the premises. Important Notice All items are sold as seen. The British Embassy makes no guarantees regarding the condition or functionality of any item and accepts no responsibility for their working status. All items won must be collected in full. Participants are not permitted to select or reject individual items from their winning bids. The British Embassy reserves the right to cancel the auction in part or in full without prior notice We welcome your interest and participation. British Embassy, Addis Ababa Comoros Street Addis Ababa, Ethiopia
Closing Date
Check Details