National Opportunities

Tender Notice Board

Discover the latest public procurement and private sector tenders from across Ethiopia. Register to unlock full details.

Search Tenders

Browse Categories

Showing 13 to 24 of 47 opportunities
Construction Raw Materialssale Recently

አዲስ ባንክ አ.ማ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ንብረቶች ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡በዚሁ መሰረት ተጫራቾች  ጨረታው በሚከናወንበት ቦታ  አዲስ ባንክ ዋና መ/ቤት ዝቋላ ህንጻ ሶስተኛ ፎቅ በመገኘት  በጨረታው መወዳደር ይችላሉ፡፡

Addis Bank

አዲስ ባንክ አ.ማ የሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ አዲስ ባንክ አ.ማ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ንብረቶች ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡በዚሁ መሰረት ተጫራቾች  ጨረታው በሚከናወንበት ቦታ  አዲስ ባንክ ዋና መ/ቤት ዝቋላ ህንጻ ሶስተኛ ፎቅ በመገኘት  በጨረታው መወዳደር ይችላሉ፡፡ ተ.ቁ መግለጫ መለኪያ የጨረታው መነሻ  ዋጋ በጥቅል  ከቫት በፊት  ብር ጨረታው የሚከናወንበት ቀንና ሰዓት 1 አልሙኒየም ፓርትሽን፣ መስታወት እና ጂፕሰም ቦርድ ባለበት ሁኔታ በጥቅል 2,590,912.23 ግንቦት12 ቀን 2018ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 2 አልሙኒየም ሼልፍ ባለበት ሁኔታ በጥቅል 448,393.43   ማሳሰቢያ ፡- ንብረቶቹን ለማየት የሚፈልጉ ተጫራቾች  ግንቦት 6፤7 እና 8 ቀን 2018ዓ.ም አዲስ ባንክ እናት ባንክ ጀርባ ኢትስዊች ህንጻ 4ኛ እና 5እኛ ፎቅ በመገኘት ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ላይ በመገኘት  ማየት ይቻላሉ፡፡ ስልክ ቁጥር  0115570319   ተጫራቾች መጫረት የሚፈልጓቸውን ንብረቶች ዝርዝር ሁኔታ የጨረታ ሰነድ ላይ የሚገኝ ሲሆን የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር ብቻ/ በአዲስ  ባንክ አ.ማ ባምቢስ ኖክ ማደያ ፊት ለፊት በሚገኘው ዝቋላ ኮምፕሌክስ ህንጻ ዓብይ ቅርንጫፍ በመክፈልና ደረሰኙን በመያዝ ከእናት ባንክ ጀርባ ኢትስዊች ህንጻ አምስተኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው   የግዥና ፋስሊቲ አስተዳደር መምሪያ ከሚያዝያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 10 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ዘወትር በስራ ስዓት ከሰኞ እስከ አርብ ጠዋት 2፡00- 6፡00፣ ከስዓት በኋላ ከ7፡00-11፡00 እንዲሁም ቅዳሜ ጠዋት 2፡00-6፡00 ማግኘት ይችላሉ፡፡ ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ግንቦት 12 ቀን እስከ ቀኑ 7፡30 ድረስ አዲስ ባንክ ዋና መ/ቤት ዝቋላ ህንጻ ሶስተኛ ፎቅ ለዚህ በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታው ማስከበሪያ  የጨረታ መነሻ  ዋጋ ¼ ወይም 25 % በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ሰነድ /ሲ.ፒ.ኦ/ በጨረታው ዕለት ይዞ በመምጣት መወዳደር ይቻላል፡፡ አሸናፊ የሚሆነው ተጫራች ያሸነፈበትን ገንዘብ በ15 /አስራ አምስት/ ተከታታይ ቀናት ውስጥ አጠቃሎ በመክፈል ንብረቶቹ ከተገጠሙበት ቦታ ነቅሎ ማንሳት ይኖርበታል፡፡ በነዚህ ቀናት ውስጥ ካልከፈለ ለጨረታ ያስዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ባንኩ ሌላ አማራጭ ይወስዳል፡፡ ጨረታውን ላላሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት የክፍያ ሰነድ አሸናፊው ከተለየ በኋላ ወዲያውኑ ይመለስላቸዋል፡፡ ጨረታው ግንቦት 12 ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ  ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት አዲስ ባንክ ዋና መ/ቤት ዝቋላ ህንጻ ሶስተኛ ፎቅ ይከፈታል፡፡ ለበለጠ ማብራሪያ አዲስ ባንክ አ.ማ ዋና መ/ቤት በስልክ ቁጥር 0115 570319 ደውሎ መረዳት ይቻላል፡፡ ባንኩ ንብረቱን ለመሸጥ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ፡፡ አዲስ ባንክ አ.ማ  

Closing Date

Check Details

Bank RelatedForeclosureIndustry & Factory ForeclosureMachine & Equipment Foreclosuresale Recently

አቢሲንያ ባንክ አ.ማ ለሰጠው ብድር በመያዣ የያዛቸውንናበሠንጠረዡ የተመለከቱትንንብረቶችበአዋጅ ቁጥር 97/90 (እንደተሻሻለው) እና 1147/2011 መሠረት ባሉበትሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።

Abyssinia Bank

የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ አቢሲንያ ባንክ አ.ማ ለሰጠው ብድር በመያዣ የያዛቸውንናበሠንጠረዡ የተመለከቱትንንብረቶችበአዋጅ ቁጥር 97/90 (እንደተሻሻለው) እና 1147/2011 መሠረት ባሉበትሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል። በመሆኑም ተጫራቾች ለጨረታ ከመቅረባቸው በፊት የሚከተሉትን ደንቦች መገንዘብ ይኖርባቸዋል። ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ንብረት የጨረታ መነሻ ዋጋውን ¼ (አንድ አራተኛ) በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይም ሲ.ፒ.ኦ በአቢሲንያ ባንክ ስም በማሰራት ለጨረታ ማስከበሪያ በማስያዝ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ። የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ ከባንኩ በደብዳቤ ከተገለጸለት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ በ15 (አስራ አምስት) ቀናት ውስጥ አጠቃሎ ከፍሎ በጨረታ ያሸነፈውን ንብረት መረከብ ይኖርበታል። በእነዚህ ቀናት ውስጥ የሚፈለግትን ክፍያ ከፍሎ ንብረቱን ካልተረከበ ጨረታው ተሰርዞ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል። በጨረታው ለተሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ሲ.ፒ.ኦ ወዲያው ይመለስላቸዋል። ተበዳሪ/መያዣ ሰጪ በሐራጁ ቀንና ሰዓት በቦታው መገኘት ይችላሉ። ነገር ግን ባይገኙ ሐራጁ በሌሉበት ይካሄዳል። የጨረታው አሸናፊ ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያያዙ ማናቸውም ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎችን፣ ግብር፣ በሽያጩ ዋጋ ላይ የሚታሰብ የተጨማሪ እሴት ታክስ 15% እንዲሁም ከስም ዝውውር ጋር የሚገናኙ ማናቸውም ወጪዎችን ይከፍላል። ንብረቶቹን በሥራ ሰዓት ፕሮግራም አስይዞ መጎብኘት ይቻላል። በባንኩ የብድር ፖሊሲ እና መመሪያ መሰረት መስፈርቱን ለሚያሟላ የጨረታው ከፍተኛ ዋጋ አቅራቢ /አሸናፊ/ ባንኩ ከፊል ብድር ሊያመቻች ይችላል። ጨረታው የሚካሄደው አዲስ አበባ ቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 7 ለገሀር በሚገኘው የአቢሲንያ ባንክ አ.ማ ዋና መስሪያ ቤት 4ኛ ፎቅየፎርክሎዠርና ዴት ሊቲጌሽን ለጨረታ ባዘጋጀው ቢሮ ውስጥ ነው። ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 011515 0711 ወይም 011 515 1153በመደወል መጠየቅ ይቻላል። ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። ማሳሰቢያ፡- መጋዘኖቹ እና ማሽነሪዎቹ ተነጣጥለው አይሸጡም። ተ.ቁ የተበዳሪው ስም የመያዣ ሰጪው ስም የንብረቱ አይነት እና አገልግሎት የቦታው አጠቃላይ ስፋት በካ.ሜ የካርታ ቁጥር ንብረቱ የሚገኝበት አድራሻ የጨረታው መነሻ ዋጋ በብር ጨረታው የሚካሄድበት ቀን የምዝገባ ሰዓት የጨረታ ሰዓት የጨረታው ሁኔታ       1.   ቡሬ የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ኃ/የተ/የግ/ማበር   ተበዳሪው ለኢንዱስትሪ/ማኑፋክቸሪንግ አገልግሎቶች የሚውሉ 3 የተለያየ ስፋት ያላቸው መጋዘኖች     30,000 (ሰላሳ ሺህ) ካ.ሜ     ገ/መ/አስ/መ14/2013     አማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላና ጠራ ወረዳ ሰርቲ ቀበሌ   የመጋዘኖቹ በድምሩ ብር 61,854,744.00   ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም   4:30-5:30     5፡30 -6፡00 በድጋሚ   ዘመናዊ የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ማሽን   —–   የደረሰኝ ቁጥር 063፣057፣076፣081 እና 053   የማሽኑ ብር 12,000,000.00     ለመጀመሪያ ጊዜ       2.   ምሳሌ አግሮ ኢንዱስትሪ ኃ/የተ/የግ/ማህበር   ተበዳሪው ለኢንዱስትሪ  አገልግሎቶች የሚውሉ 5 የተለያየ ስፋት ያላቸው መጋዘኖች     50,000 (ሀምሳ ሺህ) ካ.ሜ     ገ/መ/አስ/መ07/2013     አማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላና ጠራ ወረዳ ሰርቲ ቀበሌ     የመጋዘኖቹ በድምሩ ብር 63,735,635.18   ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም   8:30-9:30     9፡30 -10፡00     ለመጀመሪያ ጊዜ   ዘመናዊ የወተት እና የወተት ተዋጽኦ ማቀነባበሪያ ማሽን     —–   የደረሰኝ

Closing Date

Check Details

A House & Building SaleBank Relatedsale Recently

አዲስ ባንክ አ.ማ ለሰጠው ብድር ማካካሻ በአዋጅ ቁጥር 97/90 በተሰጠው ስልጣን መሠረት የተረከበውን ከዚህ በታች በሠንጠረዥ የተመለከተውን ንብረት በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡

Addis Bank

                                                                                      አዲስ ባንክ አ.ማ የሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ   አዲስ ባንክ አ.ማ ለሰጠው ብድር ማካካሻ በአዋጅ ቁጥር 97/90 በተሰጠው ስልጣን መሠረት የተረከበውን ከዚህ በታች በሠንጠረዥ የተመለከተውን ንብረት በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡በዚሁ መሰረት ተጫራቾች  ጨረታው በሚከናወንበት ቦታ በመገኘት  በጨረታው መወዳደር ይችላሉ፡፡     ተ.ቁ ንብረቱ የሚገኝበት አድራሻ   የቦታ ስፋት የንብረቱ ዓይነት የጨረታ መነሻ ዋጋ ብር ጨረታው የሚከናወንበት ቀንና ሰዓት ከተማ ክ/ከተማ   1 አዳማ ደምበላ ኢሬቻ ወረዳ 1000 ካሬ.ሜ G+4 ቅይጥ አገልግሎት 72,361,436.71 ሚያዚያ 15 ቀን 2018ዓ.ም ከሰዓት 8፡00- 9፡00 ሰዓት   ማሳሰቢያ ፡- ቤቱን ለማየት የሚፈልጉ ተጫራቾች  ሚያዝያ 8፤9 እና 10 ቀን 2018ዓ.ም አዳማ ዲስትሪክት  ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ላይ በመገኘት ንብረቱን ማየት ይቻላል፡፡ ስልክ ቁጥር 0222 111562/0115570319፡፡ የጨረታው ማስከበሪያ  የጨረታ መነሻ  ዋጋ ¼ ወይም 25 % በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ሰነድ /ሲ.ፒ.ኦ/ በጨረታው ዕለት ይዞ በመምጣት መወዳደር ይቻላል፡፡ አሸናፊ የሚሆነው ተጫራች ያሸነፈበትን ገንዘብ በ15 /አስራ አምስት/ ተካታታይ ቀናት ውስጥ አጠቃሎ መክፈል ይኖርበታል ፡፡ ጨረታውን ላላሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት የክፍያ ሰነድ አሸናፊው ከተለየ በኋላ ወዲያውኑ ይመለስላቸዋል፡፡ ጨረታው ሚያዝያ 15 ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ  ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ንብረቱ  ባለበት ቦታ ይከናወናል፡፡ ንብረቱ በገዥው ስም እንዲዘዋወር ባንኩ ለሚመለከተው መንግስታዊ አካል ደብዳቤ ይፅፋል፡፡ የጨረታው አሸናፊ ለመንግስት የሚከፈለውን አስፈላጊ ግብር እና ተጨማሪ እሴት ታክስ ይከፍላል፡፡ ባንኩ ላሸነፉ ተጫራቾች ብድር ያመቻቻል፡፡ ለበለጠ ማብራሪያ አዲስ ባንክ አ.ማ ዋና መ/ቤት በስልክ ቁጥር 0115 570319 ደውሎ መረዳት ይቻላል፡፡ ባንኩ ንብረቱን ለመሸጥ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ፡፡ አዲስ ባንክ አ.ማ  

Closing Date

Check Details

Bank RelatedDisposal SaleForeclosuresaleVehicle Foreclosure Recently

 ኦሮሚያ ባንክ አ.ማ በአዋጅ ቁጥር 1147/2011 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ለሰጠው ብድር በዋሰትና የያዘዉን በሰንጠረዡ ላይ የተዘረዘሩትን ተሽከርካሪዎችን ባሉበት በግልጽ ሐራጅ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ 

Oromia Bank

የሐራጅ ማስታወቂያ  ኦሮሚያ ባንክ አ.ማ በአዋጅ ቁጥር 1147/2011 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ለሰጠው ብድር በዋሰትና የያዘዉን በሰንጠረዡ ላይ የተዘረዘሩትን ተሽከርካሪዎችን ባሉበት በግልጽ ሐራጅ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ ተ.ቁ   የተበዳሪው ስም     የንብረት አስያዥ ስም የተሸከርካሪው አይነት የሚገኝበት አድራሻ የሰሌዳ ቁጥርና ሞተር ቁጥር     የጨረታ መነሻ ዋጋ የጨረታዉ ቀንና ሰዓት   ጨረታው የወጣው የመኪና ዓይነት የሚገኝበት ቦታ የሰሌዳ ቁጥር የተሰራበት ዘመን የሻንሲ ቁጥር የሞተር ቁጥር 1 አቶ ይድነቃቸዉ ተሰማ ወልደማርያም ተበዳሪው ህንድ-ሱዙኪ ዲዛይር   አዲስ አበባ፣ሜክሲኮ(ሰንጋ ተራ) በሚገኘው የባንኩ ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚገኝ፤ አአ-03-B79598 2022 MBHCZF63S00335952   K12MP4350817   3,020,000.00 ሚያዚያ 07 ቀን 2018 ዓ.ም ከ 3:30-4:30 ሰዓት በድጋሚ 2 አልፋ ትሬድንግ ፓርትነርስ ኃላ/የተ/የግ/ማህበር   ተበዳሪዉ ሃዩንዳይ ቫን የጭነት ተሽከርካሪ አአ-3-A19890   2014 (ኢኤ.አ)   KMFGA17CPFC284874   D4DCFJ591267   1,500,000.00 ሚያዚያ 07 ቀን 2018 ዓ.ም ከ 4:30-5:30 ሰዓት በድጋሚ   ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የጨረታውን መነሻ ዋጋ 25% በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ሰነድ/ሲ.ፒ.ኦ በኦሮሚያ ባንክ ስም አሰርተው ጨረታው በሚካሄድበት ዕለት ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ በጨረታው ከፍተኛ ዋጋ ላልሰጡ ተጫራቾች ያስያዙት ገንዘብ ወዲያዉኑ ይመለስላቸዋል፡፡ ጨረታው በሰንጠረዡ ላይ በተጠቀሰው ቀን እና ሰዓት ቦሌ መንገድ ኦሎምፒያ አካባቢ አምራን ሆቴል ጎን የኦሮሚያ ባንክ ህግ አገልግሎት ቢሮ የሚገኝበት ናትሩት ሀውስ (ህንፃ) 9ኛ ፎቅ ላይ የሚገኝ የጨረታ አዳራሽ ውስጥ ባለዕዳዎቹ ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው እና ታዛቢዎች በተገኙበት ይካሄዳል፡፡ ባለ ዕዳዎቹ ባይገኙም ጨረታው ይካሄዳል፡፡ የተጨራቾች ምዝገባ ከሐራጅ መዝግያ ስዓት 5 ደቅቃ በፊት ይጠናቀቃል፡፡ የጨረታ መጠናቀቂያ ሰዓት ድረስ ከፍተኛ ዋጋ የሰጠ ተጫራች ካልተለየ አስኪለይ ድረስ ጨረታው የሚቀጥል ይሆናል፡፡ በጨረታው ከፍተኛ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች ማሸነፉን የሚገልጽ ደብዳቤ ከባንኩ ህግ አገልግሎት ሲደርሰው ብቻ አሸናፊ ይባላል፡፡ ጨረታውን ያሸነፈ ተጫራች አሸናፊ መሆኑ በጽሁፍ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ዋጋ በ15 ቀን ውስጥ ለባንኩ አጠቃሎ ገቢ ማድረግ ይኖርበታል፡፡ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ገቢ የማያደርግ የጨረታ አሸናፊ ያስያዘው ሲፒኦ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ጨረታው ይሰረዛል፡፡ በተጨማሪም ንብረቱ በድጋሚ ለሐራጅ ሲቀርብ ለሚፈጠረው ልዩነት ይጠየቃል፡፡ በባንኩ ብድር ፖሊሲ መሰረት የሚፈለገውን ማስረጃ አሟልቶ ለቀረበ የጨረታ አሸናፊ ባንኩ ብድር ሊያመቻች ይችላል፡፡ ጨረታውን ያሸነፈ ተጫራች ንብረቱን በማስተላለፍ ሂደት ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎች፣ ግብር፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ፤ የስም ማዘወሪያ እና ማናቸዉም ከጨረታው ጋር በተገናኘ መንግስት የሚጠይቀው ታክስ ክፍያ ይከፍላል፡፡ ንብረቱ በገዢው ስም እንዲዞር ባንኩ ለሚመለከተው መንግስታዊ አካል ደብዳቤ ይጽፋል፡፡ ተጨራቾች ለጨረታ የቀረቡትን ተሽከርካሪዎች በስራ ሰዓት ፕሮግራም አስይዞ ለመጎብኘት ይችላሉ፡፡ ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 011 557 13 72 ዋና መ/ቤት ሕግ አገልግሎት፣ወይም ለተራ ቁ.1 በ 011-667-27-24 ኦሮሚያ ባንክ ቡርቃ ቅርንጫፍ፣ለተ.ቁ 2 በ 0115/504330 ቦሌ ቅርንጫፍ ደውለው መጠየቅ ይቻላል፡፡ ባንኩ ጨረታውን በማንኛውም ጊዜ በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ ኦሮሚያ ባንክ አ.ማ

Closing Date

Check Details

A House & Building SaleBank RelatedForeclosureHouse & Building Foreclosuresale Recently

ሕብረት ባንክ አ.ማ. በቅርንጫፎቹ በኩል ለሰጠው ብድር በመያዣነት የያዛቸውን እና ከዚህ በታች የተመለከቱትን ንብረቶች በአዋጅ ቁጥሮች 97/90 እና 216/92 በተሰጠው ስልጣን መሰረት በግልፅ ሐራጅ(ጨረታ) አወዳድሮ ይሸጣል፡፡

Hibret Bank

የሐራጅ ማስታወቂያ ሕብረት ባንክ አ.ማ. በቅርንጫፎቹ በኩል ለሰጠው ብድር በመያዣነት የያዛቸውን እና ከዚህ በታች የተመለከቱትን ንብረቶች በአዋጅ ቁጥሮች 97/90 እና 216/92 በተሰጠው ስልጣን መሰረት በግልፅ ሐራጅ(ጨረታ) አወዳድሮ ይሸጣል፡፡ ተራ ቁ. የተበዳሪ ስም  የአስያዥ ስም አበዳሪው ቅርንጫፍ ቤቶቹ የሚገኙበት አድራሻና የቦታ ስፋት የንብረቱ የይዞታ ማረጋገጫ ቁጥር የሐራጅ መነሻ ዋጋ በብር ሐራጁ የሚካሄድበት ቀንና ሰዓት 1 አቶ ብርሃኑ በላይ መኳንንት አቶ ብርሃኑ በላይ መኳንንት   አብነት ሞጆ ከተማ፣ቀበሌ 02፣የቦታ ስፋት 160 ካ.ሜ፣አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት 344/07 1,643,980.00 ግንቦት 04 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 5፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት 2 አቶ ፈንታሁን በዜ ሽፈራው አቶ ፈንታሁን በዜ ሽፈራው ሞጣ ጎጃም፣ሞጣ ከተማ፣ቀበሌ 01፣የቦታ ስፋት 250 ካ.ሜ፣ አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት   5005/2013 1,697,059.00   ግንቦት 04 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 5፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት 3 አቶ ይዘዘው ይላቅ ሞላ አቶ ይዘዘው ይላቅ ሞላ ገንደውሃ ጎንደር ከተማ፣ማራኪ ክፍለ ከተማ፣ቀበሌ 20፣የቦታ ስፋት 200 ካ.ሜ፣አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት 14264/11 5,410,515.00   ግንቦት 07 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 5፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት 4 ወ/ሮ ውባገኝ መልኬ ታደሰ ወ/ሮ በልጣ እጂጉ ገንደውሃ ጎንደር፣ገንደውሃ ከተማ፣ቀበሌ 02፣የቦታ ስፋት 192 ካ.ሜ፣ አገልግሎቱ ለሆቴል(ለንግድ) የሆነ  ቤት በ 279/99 716,987.00 ግንቦት 07 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ከ8፡00 እስከ 9፡00 ሰዓት 5 አቶ ነገስታት አንበርብር አወቀ አቶ ባበይ ቦጋለ እጂጉ ገንደውሃ ጎንደር፣ገንደውሃ ከተማ፣ቀበሌ 02፣የቦታ ስፋት 200 ካ.ሜ፣ አገልግሎቱ ለቅይጥ የሆነ ቤት በ=617/2011 770,376.00 ግንቦት 07 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 እስከ 10፡00 ሰዓት 6     ወ/ሮ ስምረት አብረሃ ገብረስላሴ ወይ/ ዓለምነሽ ዓሊ ገንደውሃ ጎንደር፣ገንደውሃ ከተማ፣ቀበሌ 01፣የቦታ ስፋት 200 ካ.ሜ፣ አገልግሎቱ ለንግድ የሆነ  ቤት አ=1833/2009 342,251.00 ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 5፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት ወይ/ ሃብታም ደሳለኝ ዳኘው ገንደውሃ ጎንደር፣ገንደውሃ ከተማ፣ቀበሌ 01፣የቦታ ስፋት 200 ካ.ሜ፣ አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ  ቤት ሀ=340/2009 2,027,553.00 ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ከ8፡00 እስከ 9፡00 ሰዓት 7 አቶ ፍቃዱ ለውጤ ዓለሙ አቶ ፍቃዱ ለውጤ ዓለሙ ደባርቅ ጎንደር፣ደባርቅ ከተማ፣ቀበሌ 03፣የቦታ ስፋት 250 ካ.ሜ፣ አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ  ቤት 69/960/2006 1,580,845.00 ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ከ9፡00 እስከ 10፡00 ሰዓት የሐራጅ ደንቦች፡- የሐራጁን መነሻ ዋጋ አንድ አራተኛ በሕብረት ባንክ አ.ማ.(Hibret Bank C) ስም የተሰራ የባንክ ክፍያ ማዘዣ(ሲ.ፒ.ኦ.) ብቻ በማስያዝ መጫረት ይችላሉ፡፡ከባንክ ክፍያ ማዘዣ(ሲ.ፒ.ኦ) ውጭ የሚቀርብ የጨረታ ማስያዣ ተቀባይነት የለውም፡፡ ለሐራጅ የቀረበውን ንብረት ለመጎብኘት የሚፈልግ ተጫራች ከቅርንጫፎቹ ወይም ከሕግ አገልግሎት መምሪያ ጋር አስቀድሞ ቀጠሮ በመያዝ ከጨረታው ዕለት ሶስት ቀናት አስቀድሞ መጎብኘት ይችላል፡፡ በሐራጅ ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች፣ተበዳሪ እና አስያዥ ብቻ ናቸው፡፡ተጫራቾች በሐራጅ ለመሳተፍ ሲመጡ መታወቂያ መያዝ ይገባቸዋል፡፡ተጫራቾች የሕግ ሰውነት የተሰጣቸው አካላት ከሆኑ ደግሞ ሕጋዊ ሰውነት ያገኙበትን የዋና ምዝገባ ምስክር ወረቀት እና ሐራጁን ለመሳተፍ የቀረበው ሰው ስልጣኑን የሚያሳይ በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ወይም በተመሳሳይ አካል የፀደቀ መመስረቻ ፅሁፍ(የመተዳደሪያ ደንብ)፣ቃለ ጉባኤ ወይም የውክልና ሰነድ ይዞ መቅረብ አለበት፡፡ በተራ ቁጥር 1 የተጠቀሰው ንብረት ሐራጅ የሚካሄደው ንብ

Closing Date

Check Details

Food & Beveragesale Recently

ዳሽን ቢራ ፋብሪካ አ.ማ አሶሳ፣ ጎዴ፣ ፍላቂት ገረገራ እና አዲግራት መስመር የዳሽን ቢራ ምርቶችን ለማከፋፈል ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡

Dashen Breweries S.C

ዳሽን ቢራ ፋብሪካ አ.ማ አሶሳ፣ ጎዴ፣ ፍላቂት ገረገራ እና አዲግራት መስመር የዳሽን ቢራ ምርቶችን ለማከፋፈል ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም፡- በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያለው በቂ ተሽከርካሪ ማቅረብ የሚችል (የራሱ ቢሆን ይመረጣል) ምርቱን ለማከማቸት የሚሆን መጋዘን (የራሱ ቢሆን ይመረጣል) በዘርፉ ተዛማጅ የስራ ልምድ ያለው የስራ ማስኬጃ በቂ ካፒታል ያለው መሆኑን የሚያሳይ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ በአካባቢው ለረጅም ጊዜ ነዋሪ የሆነና በአካባቢው ማህበረሰብ መልካም ስም ያላቸው፤ ማህበራዊ እና ህጋዊ ግዴታዎችን በአግባቡ እየተወጣ ያለና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤ ተጫራቾች ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 7 (ሰባት) ተከታታይ ቀናት ውስጥ አስፈላጊውን ሠነድ አሟልተው አዲስ አበባ፣ ዳሽን ቢራ ፋብሪካ ዋና መስሪያ ቤት (22 የቱሪስት ንግድ ስራ ድርጅት አጠገብ) ከሚገኘው የድርጅቱ ቢሮ ለዚህ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በብር 1000 (አንድ ሺ ብር) ገዝቶ በመሙላት ጨረታውን መሳተፍ የሚችሉ መሆኑን እየገለጽን:: ጨረታው ከመጋቢት 09 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 25 2018 ዓ.ም ድረስ አየር ላይ የሚቆይ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ ጨረታው መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ/ም ጠዋት 4:00 ተዘግቶ በዚያው እለት 4፡30 የሚከፈት ሲሆን ቀጣይ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) ቀናት ውስጥ ውጤቱን የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ ዳሽን ቢራ ፋብሪካ አ.ማ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብት አለው፡፡ ከሠላምታ ጋር

Closing Date

Check Details

Food & Beveragesale Recently

ዳሽን ቢራ ፋብሪካ አ.ማ አሶሳ፣ ጎዴ፣ ፍላቂት ገረገራ እና አዲግራት መስመር የዳሽን ቢራ ምርቶችን ለማከፋፈል ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡

Dashen Breweries S.C

ዳሽን ቢራ ፋብሪካ አ.ማ አሶሳ፣ ጎዴ፣ ፍላቂት ገረገራ እና አዲግራት መስመር የዳሽን ቢራ ምርቶችን ለማከፋፈል ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም፡- በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያለው በቂ ተሽከርካሪ ማቅረብ የሚችል (የራሱ ቢሆን ይመረጣል) ምርቱን ለማከማቸት የሚሆን መጋዘን (የራሱ ቢሆን ይመረጣል) በዘርፉ ተዛማጅ የስራ ልምድ ያለው የስራ ማስኬጃ በቂ ካፒታል ያለው መሆኑን የሚያሳይ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ በአካባቢው ለረጅም ጊዜ ነዋሪ የሆነና በአካባቢው ማህበረሰብ መልካም ስም ያላቸው፤ ማህበራዊ እና ህጋዊ ግዴታዎችን በአግባቡ እየተወጣ ያለና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤ ተጫራቾች ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 7 (ሰባት) ተከታታይ ቀናት ውስጥ አስፈላጊውን ሠነድ አሟልተው አዲስ አበባ፣ ዳሽን ቢራ ፋብሪካ ዋና መስሪያ ቤት (22 የቱሪስት ንግድ ስራ ድርጅት አጠገብ) ከሚገኘው የድርጅቱ ቢሮ ለዚህ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በብር 1000 (አንድ ሺ ብር) ገዝቶ በመሙላት ጨረታውን መሳተፍ የሚችሉ መሆኑን እየገለጽን:: ጨረታው ከመጋቢት 09 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 25 2018 ዓ.ም ድረስ አየር ላይ የሚቆይ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ ጨረታው መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ/ም ጠዋት 4:00 ተዘግቶ በዚያው እለት 4፡30 የሚከፈት ሲሆን ቀጣይ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) ቀናት ውስጥ ውጤቱን የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ ዳሽን ቢራ ፋብሪካ አ.ማ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብት አለው፡፡ ከሠላምታ ጋር  

Closing Date

Check Details

A House & Building SaleBank RelatedForeclosureHouse & Building Foreclosuresale Recently

ፀደይ ባንክ አ.ማ ለምቾት ኃ/የተ/የግ/ማህበር  ለሰጠው ብድር በመያዣ የያዛቸውንና ዝርዝር ሁኔታቸው ከዚህ በታች የተገለጹትን ንብረቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡

Tsedey Bank S.C

         ለ2ኛ ጊዜ የወጣ የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ ፀደይ ባንክ አ.ማ ለምቾት ኃ/የተ/የግ/ማህበር  ለሰጠው ብድር በመያዣ የያዛቸውንና ዝርዝር ሁኔታቸው ከዚህ በታች የተገለጹትን ንብረቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ ተ.ቁ የተበዳሪ ስም የንብረት አስያዥ ስም የንብረቱ መገኛ እና ካርታ ቁጥር መነሻ ግምት 1 ምቾት  ኃ/የተ/የግ/ ማህበር አቶ ታፈረ ወርቁ መራ በአብክመ በቡሬ ከተማ ቀበሌ03  የሚገኝ ካርታ  ቁጥር 16421/2013 መኖሪያ ቤት 2,487,661.37 2 ምቾት  ኃ/የተ/የግ/ ማህበር  አቶ ታፈረ ወርቁ መራ በአብክመ በቡሬ ከተማ ቀበሌ  02 የሚገኝ ካርታ  ቁጥር 16422/2013 መኖሪያ ቤት 1,831,779.94 3 ምቾት  ኃ/የተ/የግ/ ማህበር አቶ ታፈረ ወርቁ መራ በአብክመ በቡሬ ከተማ ቀበሌ  02 የሚገኝ ካርታ  ቁጥር 9005//2008 መኖሪያ ቤት 2,119,342.42 በመሆኑም ማንኛቸውም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ደንቦችና ቅድመ ሁኔታዎች ማሟላት የሚችሉ ተጫራቾች በጫራታው እንዲሳተፉ እንጋብዛለን፡፡ ተጫራቾች የቤቱን የጨረታ መነሻ ዋጋ ¼ (በጥሬ ገንዘብ ወይም በሲፒኦ) በፀደይ ባንክ አ.ማ ስም በማሰራት ለጨረታ መስከበሪያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል በጨረታው የሚሳተፈው በሕግ ሰውነት ያገኘ ሰው ከሆነ የድርጅቱን መመስረቻ ጽሑፍ ወይም መተዳደሪያ ደንብ ፤ሕጋዊ ሰውነት ያገኘበትን የምዝገባ የምስክር ወረቀት እንዲሁም ሕጋዊ ውክልና ማቅረብ ይኖርበታል የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ የሚረጋገጠው የጨረታው ውጤት በሚመለከተው አካል ጸድቆ በባንኩ ደብዳቤ ሲሰጠው ይሆናል የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ በባንኩ በደብዳቤ ከተገለጸለት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ በ15 ቀናት ውስጥ አጠቃሎ መክፈልና በጨረታ ያሸነፈውን ንብረት መረከብ ይኖርበታል፡፡ አሸናፊው በ15 ቀናት ውስጥ ገንዘቡን ካልከፈለ ጨረታው ተሰርዞ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ያሆናል፡፡ በጨረታው ለተሸነፉ ተጫራቾች ያስያዙት ይመለስላቸዋል የጨረታ አሸናፊው ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያያዙ ማናቸውም ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎች ፣ግብር፤ የተጨማሪ እሴት ታክስ 15% የሚከፈል ከሆነ እንዲሁም ከስም ዝውውር ጋር የሚገናኙ ማንኛውንም ወጭዎች ይሸፍናል፡፡ ውዝፍ የሊዝ ክፍያ ካለ ባንኩ የሚከፍል ሆኖ ለቀረው የሊዝ ክፍያ ገዡ ከሚመለከተው የመንግስት አካል ጋር ይዋዋላል፡፡ ተጫራቾች ቤቱን በባንኩ አማካኝነት መጎብኘት ወይም ማየት ይችላሉ ጨረታው ግንቦት 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 3፡00 እስከ 6፡00 ፍኖተሰላም ከተማ ከሚገኘው የፀደይ ባንክ ፍኖተ ሰላም ዲስትሪክት ቢሮ ግራውንድ ይደረጋል ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0918560275

Closing Date

Check Details

A House & Building SaleBank RelatedForeclosureHouse & Building Foreclosuresale Recently

ወጋገን ባንክ አ.ማ ከታች በሰንጠረዡ የተጠቀሰውን መኖሪያ ቤት ለሰጠው ብድር በእዳ ማካካሻነት ይዞት የነበረ እና አሁን በእዳ የተረከበው በመሆኑ ባለበት ሁኔታ በዝግ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።

Wegagen bank

  የጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ ቁጥር WB/PAF/06/26 ወጋገን ባንክ አ.ማ ከታች በሰንጠረዡ የተጠቀሰውን መኖሪያ ቤት ለሰጠው ብድር በእዳ ማካካሻነት ይዞት የነበረ እና አሁን በእዳ የተረከበው በመሆኑ ባለበት ሁኔታ በዝግ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል። የንብረቱ ዓይነት ንብረቱ የሚገኝበት አድራሻ የጨረታ መነሻ ዋጋ ብር ቤቱ/ሕንጻው ያረፈበት ቦታ በካ.ሜ ይዞታው ጠቅላላ ስፋት ከተማ ክ/ከተማ የቦታው ልዩ ስም የካርታ ቁጥር G+1 መኖሪያ ቤት ኦሮሚያ ሸገር ከተማ ለገጣፎ ለገዳዲ CCD (Country Club Developers) ግቢ ውስጥ OR042030709006 26,100,000.00 ምድር ቤት 259.95 ካ.ሜ 1ኛ ወለል 220.01 ካ.ሜ ሰርቪስ ቤት 54.10 ካ.ሜ 1,022.06 ካ.ሜ ማሳሰቢያ ተጫራቾች ከየትኛውም የወጋገን ባንክ ቅርንጫፍ የተጨማሪ እሴት ታክስ ጨምሮ ብር 00 (ሶስት መቶ አርባ አምስት ብር) በሒሳብ ቁጥር 0736452410101 በተጫራቹ ስም ገቢ በማድረግ ገቢ የሆነበትን ደረሰኝ በመያዝ የጨረታው ሰነድ የባንኩ ዋና መ/ቤት ወጋገን ሕንጻ 3ኛ ወለል ንብረት አስተዳደር እና ፋሲሊቲስ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ሚያዝያ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ መግዛትና መወዳደር ይችላሉ፡፡   የመኖሪያ ቤቱን ለመጎብኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ባንኩ በሚያወጣው መርሐ-ግብር መሰረት መጎብኘት ይችላሉ፡፡   ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው መኖሪያ ቤቱን የሚገዙቡትን ዋጋ ¼ኛ (ሃያ አምስት በመቶ) ለጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ ሲ.ፒ.ኦ (CPO) በወጋገን ባንክ አ.ማ ስም አሰርተው ከጨረታው ሰነድ ጋር በታሸገ ኢንቨሎፕ ከነሙሉ አድራሻቸው እስከ ሚያዝያ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. 8፡00 ሰዓት ድረስ አዲስ አበባ ስታዲየም ፊት ለፊት በሚገኘው የባንኩ ዋና መ/ቤት ወጋገን ሕንጻ 3ኛ ወለል ንብረት አስተዳደር እና ፋሲሊቲስ ዳይሬክቶሬት ቢሮ በመቅረብ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል። በጨረታ ሰነዱ ላይ የተጫራቹ ስም፣ፊርማ እና ስልክ ቁጥር መጻፍ አለበት። ከጨረታው ሳጥን መዝጊያ ሰዓት በኋላ የሚደርሱ የመጫረቻ ሰነዶች ተቀባይነት አይኖራቸውም። ተጫራቾች የሚያቀርቡትን የመጫረቻ ዋጋ በቀላሉ በሚጠፋ ወይም በእርሳስ መሙላት የለባቸውም። የሚሰጡት ዋጋ ላይ ስርዝ ድልዝ ካለ ከጎኑ በተጫራቹ መፈረም አለበት። አንድ ተጫራች ሌላው በሰጠው ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይችልም። ማንኛውም ተጫራች በጨረታው ተካፋይ ሆኖ ጨረታው ከተከፈተ በኋላ የሰጠውን ዋጋ መለወጥ ወይም ማሻሻል አይችልም፤ተጫራቾች ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ከውድድሩ ሊወጡ አይችሉም፡፡   ጨረታው ሚያዝያ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በእለቱ ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ወጋገን ባንክ አ.ማ. ዋና መስሪያ ቤት ሕንጻ 9ኛ ወለል በባንኩ አዳራሽ ይከፈታል፡፡     የጨረታው አሸናፊ ከመኖሪያ ቤቱ ጋር የተያያዙ ማንኛውንም ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎችን፤ ተጫራች ባቀረበው ዋጋ ላይ የሚታሰብ ግብር፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ካለ፣ ከስም ማዛወሪያ ክፍያ ጋር የተገናኙ ወጪዎች፣ውዝፍ ክፍያዎች እና ሌሎች በሕግ የተወሰኑ ወጭዎች የጨረታው አሸናፊ የሚከፈል ይሆናል፡፡   የጨረታ አሸናፊ አሸናፊነቱን ከባንኩ በደብዳቤ ከተገለጸለት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር 15 (አስራ አምስት) ቀናት ውስጥ ቀሪውን ገንዘብ አጠናቆ ከፍሎ ንብረቱን የመረከብ ግዴታ አለበት። በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ቀሪውን ገንዘብ ከፍሎ ንብረቱን የማይረከብ ተጫራች የጨረታው ውጤት ተሰርዞ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል፡፡   በጨረታው ለተሸነፉት ተጫራቾች ማለትም እስከ 3ኛ ደረጃ ያልወጡ የጨረታ ግም

Closing Date

Check Details

Disposal SalePoultry/ Bee & Animal Husbandrysale Recently

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ከሚያዝያ 01 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም  ከሚታረዱ የዳልጋ ከብት የሚገኝውን እርጥብ ቆዳ፣ ከበጎች እና ፍየሎች የሚገኝው እርጥብ ሌጦ፣ የስጋና አጥንት መኖ፣ የዳልጋ ከብት ቀንድ እና ለሳሙና መስሪያ ግብዓት የሚሆነውን የተነጠረ ሞራ  በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡

Addis Ababa abattoiers

የተረፈ ምርት ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ከሚያዝያ 01 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም  ከሚታረዱ የዳልጋ ከብት የሚገኝውን እርጥብ ቆዳ፣ ከበጎች እና ፍየሎች የሚገኝው እርጥብ ሌጦ፣ የስጋና አጥንት መኖ፣ የዳልጋ ከብት ቀንድ እና ለሳሙና መስሪያ ግብዓት የሚሆነውን የተነጠረ ሞራ  በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ማንኛውም ተጫራች፡- በመስኩ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ እና የግብር ከፋይ ሰርተፍኬት ያለውና የዘመኑን ግብር የከፈለ ማስረጃ ኮፒ ማያያዝ አለበት፡፡ የጨረታ ማስከበሪያን በተመለከተ ለዳልጋ ከብት ቆዳ የጨረታ ማስከበሪያን የሚሆን ለሦስት የጨረታ ጊዜ ለእያንዳንዱ ብር 400,000.00 (አራት መቶ ሺህ ብር)  እና በወር ውስጥ ለሚገኝው የበግና ፍየል ሌጦ የጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ብር 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) ማስያዝ ያለበት ሲሆን የዳልጋ ከብት ቆዳ ጨረታ ያሸነፈ ማንኛውም ተጫራች የቅድመ ክፍያ ለ10 ቀናት ብር 4,000,000.00 (አራት ሚሊዮን ብር) እና  የበግና ፍየል ሌጦ ያሸነፈ ማንኛውም ተጫራች የቅድመ ክፍያ ብር 500,000.00 (አምስት መቶ ሺህ ብር) በጥሬ ገንዘብ መሰብሰቢያ ደረሰኝ ወይም በሲ.ፒ.ኦ ብቻ መክፈል የሚችል መሆን አለበት፡፡ ለስጋና አጥንት መኖ የጨረታ ማስከበሪያ ለሦስቱ የጨረታ ጊዜ ለእያንዳንዱ ብር 20,000.00 (ሃያ ሺህ ብር) ለዳልጋ ከብት ቀንድ የጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ብር 10,000.00 (አስር ሺህ ብር) እና ለተነጠረ ሞራ ለሦስቱ የጨረታ ጊዜ ለእያንዳንዱ ብር 300,000.00 (ሦስት መቶ ሺህ ብር) በጥሬ ገንዘብ መሰብሰቢያ ደረሰኝ ወይም በሲ.ፒ.ኦ ብቻ ማስያዝ ይኖርበታል፡፡ ጨረታውን ያሸነፈ ማንኛውም ተጫራች ለዳልጋ ከብት ቀንድ ምርቱን በሳምንት ሁለት ቀን   እንዲሁም ለስጋና አጥንት መኖ ምርቱ በሚመረትበት በሳምንት ሦስት ቀን (ሰኞ፣ማክሰኞ እና ሐሙስ) እና ለተነጠረ ሞራ ምርቱ በተመረተበት ቀን ሙሉ በሙሉ የእጅ በእጅ ሽያጭ በማከናወን ማንሳት የሚችል መሆን አለበት፡፡ ምርቱን ለመግዛት የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች በጨረታ መመሪያ ላይ በተገለፀው መሰረት ይሆናል፡፡ አሸናፊው የሚኖረው መብትና ግዴታዎች በውል ውስጥ የሚካተት ይሆናል፡፡ ከቆዳና ሌጦ ውጪ ላሉት ምርቶች የተዘጋጀውን የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ ብር 300.00 (ሦስት መቶ ብር) በመክፈል ከድርጅቱ ማርኬቲንግ የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 2 መግዛት ይቻላል፡፡ ጨረታው ለዳልጋ ከብት ቆዳ እና ለበጎች እና ፍየሎች እርጥብ ሌጦ መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ.ም፣ ለስጋና አጥንት መኖ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም፣ ለዳልጋ ከብት ቀንድ መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም እና ለተነጠረ ሞራ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በተመሳሳይ ሰዓት 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በዚያው ዕለት 4:30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ  ይከፈታል፡፡ ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 01114-163978 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት!!!  

Closing Date

Check Details

Disposal SalePoultry/ Bee & Animal Husbandrysale Recently

አዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ከሚያዝያ 01 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም  ከሚታረዱ የዳልጋ ከብት የሚገኝውን እርጥብ ቆዳ፣ ከበጎች እና ፍየሎች የሚገኝው እርጥብ ሌጦ፣ የስጋና አጥንት መኖ፣ የዳልጋ ከብት ቀንድ እና ለሳሙና መስሪያ ግብዓት የሚሆነውን የተነጠረ ሞራ  በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡

Addis Ababa abattoiers

የተረፈ ምርት ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ከሚያዝያ 01 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም  ከሚታረዱ የዳልጋ ከብት የሚገኝውን እርጥብ ቆዳ፣ ከበጎች እና ፍየሎች የሚገኝው እርጥብ ሌጦ፣ የስጋና አጥንት መኖ፣ የዳልጋ ከብት ቀንድ እና ለሳሙና መስሪያ ግብዓት የሚሆነውን የተነጠረ ሞራ  በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ማንኛውም ተጫራች፡- በመስኩ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ እና የግብር ከፋይ ሰርተፍኬት ያለውና የዘመኑን ግብር የከፈለ ማስረጃ ኮፒ ማያያዝ አለበት፡፡ የጨረታ ማስከበሪያን በተመለከተ ለዳልጋ ከብት ቆዳ የጨረታ ማስከበሪያን የሚሆን ለሦስት የጨረታ ጊዜ ለእያንዳንዱ ብር 400,000.00 (አራት መቶ ሺህ ብር)  እና በወር ውስጥ ለሚገኝው የበግና ፍየል ሌጦ የጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ብር 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) ማስያዝ ያለበት ሲሆን የዳልጋ ከብት ቆዳ ጨረታ ያሸነፈ ማንኛውም ተጫራች የቅድመ ክፍያ ለ10 ቀናት ብር 4,000,000.00 (አራት ሚሊዮን ብር) እና  የበግና ፍየል ሌጦ ያሸነፈ ማንኛውም ተጫራች የቅድመ ክፍያ ብር 500,000.00 (አምስት መቶ ሺህ ብር) በጥሬ ገንዘብ መሰብሰቢያ ደረሰኝ ወይም በሲ.ፒ.ኦ ብቻ መክፈል የሚችል መሆን አለበት፡፡ ለስጋና አጥንት መኖ የጨረታ ማስከበሪያ ለሦስቱ የጨረታ ጊዜ ለእያንዳንዱ ብር 20,000.00 (ሃያ ሺህ ብር) ለዳልጋ ከብት ቀንድ የጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ብር 10,000.00 (አስር ሺህ ብር) እና ለተነጠረ ሞራ ለሦስቱ የጨረታ ጊዜ ለእያንዳንዱ ብር 300,000.00 (ሦስት መቶ ሺህ ብር) በጥሬ ገንዘብ መሰብሰቢያ ደረሰኝ ወይም በሲ.ፒ.ኦ ብቻ ማስያዝ ይኖርበታል፡፡ ጨረታውን ያሸነፈ ማንኛውም ተጫራች ለዳልጋ ከብት ቀንድ ምርቱን በሳምንት ሁለት ቀን   እንዲሁም ለስጋና አጥንት መኖ ምርቱ በሚመረትበት በሳምንት ሦስት ቀን (ሰኞ፣ማክሰኞ እና ሐሙስ) እና ለተነጠረ ሞራ ምርቱ በተመረተበት ቀን ሙሉ በሙሉ የእጅ በእጅ ሽያጭ በማከናወን ማንሳት የሚችል መሆን አለበት፡፡ ምርቱን ለመግዛት የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች በጨረታ መመሪያ ላይ በተገለፀው መሰረት ይሆናል፡፡ አሸናፊው የሚኖረው መብትና ግዴታዎች በውል ውስጥ የሚካተት ይሆናል፡፡ ከቆዳና ሌጦ ውጪ ላሉት ምርቶች የተዘጋጀውን የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ ብር 300.00 (ሦስት መቶ ብር) በመክፈል ከድርጅቱ ማርኬቲንግ የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 2 መግዛት ይቻላል፡፡ ጨረታው ለዳልጋ ከብት ቆዳ እና ለበጎች እና ፍየሎች እርጥብ ሌጦ መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ.ም፣ ለስጋና አጥንት መኖ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም፣ ለዳልጋ ከብት ቀንድ መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም እና ለተነጠረ ሞራ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በተመሳሳይ ሰዓት 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በዚያው ዕለት 4:30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ  ይከፈታል፡፡ ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 01114-163978 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት!!!

Closing Date

Check Details

Agricultural Machinerysale Recently

የእህል ማበጠሪያ ማሽን ሽያጭ ጨረታ ድርጅታችን ቫላም ግሎባል ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማ ቱርክ ሰራሽ የእህል ማበጠሪያ እና ማቀነባበሪያ ማሽነሪዎች ማለትም፤ ቅድመ ማበጠሪያ ማሽን ፤ዲስቶነር (ድንጋያማ ቆሻሻ መለያ) ፤ግራቪቲ መለያ ማሽን፤ የተበጠረ ማጠረቀሚያ ቋቶችና የመስፊያ ማሽን፤ የተለያዩ ለማሽኑ ያሚያስፈለጉ መሳሪያዎች…. የመሳሰሉትን በአሉበት ሁኔታ ድርጅታችን በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይ

Valam Global Trading

በመሆኑም ማሽኖቹን ለመግዛት የሚፈልግ ተጫራች በጽሁፍ የተዘጋጀውን ዝርዝር የማሽን ዓይነት በመውሰድ ማሽኖቹን በመመልከትና የመግዣ ዋጋ  (ተጨማሪ እሴት ታክስ በፊት) በታሸገ እንቨሎፕ ከአስር በመቶ የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ጋር አያይዞ ማቅረብ ይኖርብታል፡፡ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለአስራ አምስት ተከታታይ ቀናት ለተጫራቾች ክፍት ሆኖ የሚቆይ ይሆናል፡፡ በአስራ ስድስተኛው እለት ጨረታው ተዘግቶ በእለቱ ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከጠዋቱ በአራት ሰዓት ይከፈታል፡፡ አስራ ስድስተኛው ቀን በዓል ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን ላይ ይከፈታል፡፡ የጨረታውን ዶክመንት ለመውሰድና ማሽኖቹን ለማየት በሞባይል ቁጥር 0930175834፤0930175835 እና 0910314271 ላይ በመደወል መረጃ ማግኘት ይቻላል፡፡ ድርጅቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው!! ቫላም ግሎባል ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማ

Closing Date

Check Details